አዲስ ጊዜ

227 Posts
ስደተኞችን በማስጠለል ከአፍሪካ ቀዳሚ የነበረችው ኢትዮጵያ በ3ኛነት                       ተቀመጠች::

ስደተኞችን በማስጠለል ከአፍሪካ ቀዳሚ የነበረችው ኢትዮጵያ በ3ኛነት ተቀመጠች::

ለበርካታ ዓመታት በአፍሪካ በአንደኝነት ደረጃ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ስደተኛ አስጠልላ የቆየችው ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ሶስተኛዋ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ስደተኛ ተጠልሎባት የሚገኝ ሀገር ናት ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታወቀ። ሱዳንን እና ኡጋንዳን በመከተል በሶስተኝነት ስደተኞችን ያስጠለለችው ኢትዮጵያ 954ሺ ከተለያዩ ሀገራት ድንበሯን አቋርጠው የገቡ ስደተኞች እንደሚገኙባት ተቋሙ ይፋ ባደረገው መረጃ ጠቁሟል። የመንግስታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት ዩኤንኤችሲአር ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያመላክተው በኢትዮጵያ ተጠልለው ከሚገኙ ስደተኞች መካከል ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዙት ሱዳናውያን ናቸው። ከሶማሊያ እና ከኤርትራ ተሰደው በኢትዮጵያ የተጠለሉ ስደተኞች በሁለተኝነት እና በሶስተኝነት ተቀምጠዋል። ኢትዮጵያ በሁሉም ድንበሮቿ የጎረቤት ሀገራት ስደተኞች እንዲገቡ በሮቿን ክፍት ማድረጓን የጠቆመው የመንግስታቱ…
ተጨማሪ ያንብቡ
ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ወደ ሳዑዲ አረቢያ አቀኑ

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ወደ ሳዑዲ አረቢያ አቀኑ

ኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሳዑዲ አረቢያ የአፍሪካ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ወደሪያድ አቅንተዋል። የአገሪቱ የመረጃ ሚኒስትር የማነ ገብረ መስቀል በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው እንዳሰፈሩት ኢሳያስ ዛሬ ማለዳ ላይ ወደ ሳዑዲ አምርተዋል። አብረዋቸው ከተጓዙ የልዑካን ቡድናቸው አባላት መካከል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸው ኦስማን ሳለህ፥ የፓርቲያቸው የምጣኔ ኃብት ጉዳዮች ኃላፊ ሃጎስ ገብረህይወት እንዲሁም የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ነስረዲን ቤኪት ይገኙበታል። በጉባዔው ይታደማሉ ተብሎ ከሚጠበቁ ሌሎች የአፍሪካ መሪዎች መካከልም የኬንያው ዊሊያም ሩቶ እና የናይጄሪያው ቦላ ቲኑቡ ይገኙበታል። የሳዑዲ አረቢያ የአፍሪካ ጉባዔ ሪያድ ከተለያዩ የአህጉሪቷ አገራት እንዲሁም የአፍሪካ ኅብረትን ከመሳሰሉ ተቋማት ጋር ያላትን ግንኙነት የምታጠናክርበት ነው። ጉባኤው ተፋፍሞ የቀጠለው የጋዛ ቀውስ ጥላ ያጠላበታል ተብሎ…
ተጨማሪ ያንብቡ
የምክክር ኮሚሽኑ በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች እና በስድስት ክልሎች የተሳታፊዎች ልየታ መጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

የምክክር ኮሚሽኑ በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች እና በስድስት ክልሎች የተሳታፊዎች ልየታ መጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

ባለፉት 4 ወራት አዲስ አበባና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ በ6 ክልሎች የሃገራዊ ምክክር የተሳታፊዎች ልየታ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ሃገራዊ የምክክር ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ ኮሚሽኑ የ4 ወራት አፈጻጸም ረፖርቱን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት ያካሄደ ሲሆን  የኢትዮጵያ ሃገራዊ የምክክር ኮሚሽን የ4 ወራት አፈጻጸም ሪፖርትንም አዳምጧል፡፡ ምክክሩን ውጤታማ ለማድረግ በቅድመ ዝግጅት ስራው ከእድሮች፣ ከሃማኖት ተቋማት፣ ከሲቪክ ማህበራት፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች እና ከመምህራን ማህበር ጋር በአጋርነት እየሰራ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በመላ ሃገሪቱ እየተካሄደ ባለው የተሳታፊዎች ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ተግባር ሁለቱን ከተማ አስተዳደሮች ጨምሮ በ6 ክልሎች  ላይ በተለይ የልየታ ስራው…
ተጨማሪ ያንብቡ
አምስተኛው ዙር የኢትዮጵያ የሥነ-ሕዝብ እና ጤና ጥናት በሚቀጥሉት 3 ዓመታት ውስጥ ይካሄዳል ተባለ ::

አምስተኛው ዙር የኢትዮጵያ የሥነ-ሕዝብ እና ጤና ጥናት በሚቀጥሉት 3 ዓመታት ውስጥ ይካሄዳል ተባለ ::

በአሸናፊ አሰበ የኢትዮጵያ የሥነ ሕዝብና ጤና ዳሰሳ ጥናት በየአምስት አመቱ የሚካሄድ ሲሆን አራተኛው ጥናት እ.አ.አ በ2016 ከወጣ በኋላ ሳይወጣ ቆይቷል። የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት በበኩሉ አምስተኛው ዙር የሥነ ሕዝብና ጤና ዳሰሳ ጥናት በኮቪድ እና ሌሎች ልዩ ልዩ ምክንያቶች መሰራት ከነበረበት ጊዜ በሁለት ዓመት መጓተቱን ገልጾ በተያዘው በጀት ዓመት መጋቢት ወር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ ለመስራት አቅዶ እየተንቀሳቀስ እንደሆነ የአገልግሎቱ የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ እና የመረጃ ስርጭት ዳይሬክተር አቶ ሳፊ ገመዲ ለአዲስ ጊዜ ገልጸዋል። ከ2016 እስከ 2018 ዓ.ም በሚቆየው የስታቲስቲክስ ልማት ፕሮግራም ትግበራ ወቅት በሚካሄዱት ቆጠራዎችና ጥናቶችን በሚመለከት ሲከናወኑ በነበሩ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን የኢትዮጵያ…
ተጨማሪ ያንብቡ
የምግብ ድጋፍ አቅርቦት እገዳ ባለመነሳቱ በምግብ እጥረትና ሰብአዊ ቀውስ ላይ ያሳደረው ጫና እንደቀጠለ ነው።

የምግብ ድጋፍ አቅርቦት እገዳ ባለመነሳቱ በምግብ እጥረትና ሰብአዊ ቀውስ ላይ ያሳደረው ጫና እንደቀጠለ ነው።

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን(ኢሰመኮ) ለተፈናቃዮች እየቀረበ ያለውን የምግብ ድጋፍ አስመልክቶ  መግለጫ አውጥቷል፡፡  የአሜሪካ የዓለም አቀፍ ልማት ድርጅት (USAID) እና የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ከጥቅምት ወር 2016 ዓ.ም. ጀምሮ የምግብ ድጋፍ ለስደተኞች እንዲጀመር ማድረጋቸው በጎ እርምጃ ሆኖ፤ በአንጻሩ ለተፈናቃዮች እና ለሌሎች ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች የሚሰጠው የምግብ ድጋፍ አቅርቦት እገዳ  አለመነሳቱ በምግብ እጥረትና ሰብአዊ ቀውስ ላይ ያሳደረው ጫና እንደቀጠለ ነው ብሏል::የፌዴራል አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በበኩሉ የተሟላ እና በቂ ሰብአዊ ድጋፍ ለማድረግ ከፍተኛ የገንዘብ እጥረት ቢኖርም፣ ባለፉት ወራት በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ላሉ ተፈናቃዮች ትኩረት በመስጠት በሁለት ዙር በአፋር ክልል 96%፣ በጋምቤላ 96%፣ በትግራይ 87%፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ 73%፣…
ተጨማሪ ያንብቡ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዘመናዊ ቆጣሪዎችን እየቀየረ ነው።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዘመናዊ ቆጣሪዎችን እየቀየረ ነው።

በአሸናፊ አሰበ ደምበኞች በቀላሉ አፕልኬሽኑን ሞባይላቸዉ ላይ በመጫን ያላቸዉን ወርሃዊ የፍጆታ ሂሳብ በቀላሉ ለማወቅ፣ ከቆጣሪ ንባብ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ቅሬታዎችን  ለማስቀረት፣ የሃይል ስርቆትን ለመከላከል፣ የንባብ ስህተት ችግርን ለመቅረፍ እና ለመከላከል እንደሚያስችል የተነገረለት የዘመናዊ ቆጣሪ ቅየራ ስራ ሁለተኛ ዙር እንደተጀመረ  የፕሮጀክቱ ሃላፊ አቶ ጩመላ ሣሙኤል ለአዲስ ጊዜ ተናግረዋል። የመጀመሪያው ትግበራ ሚያዚያ 2015 ዓም መጀመሩን እና በሙከራው ሂደት 5000 የስማርት ቆጣሪዎችን ማዳረስ መቻሉን የተናገሩት አቶ ሣሙኤል የፕሮጀክቱ ትግበራ በዋናነት የተጀመረው ከፍተኛ ሃይል ተጠቃሚ በሆኑ ወይም የሃይል ፍጆታቸው ከ 25 ኪሎ ዋት(KW) በላይ በሚጠቀሙ የማሕበረሰብ ክፍሎች ላይ ሲሆን በሁለተኛው ዙር ትግበራ 45 ሺህ ነባር ቆጣሪዎችን በ6 ወር ጊዜ ውስጥ…
ተጨማሪ ያንብቡ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ስምንት አባላት ያሉት የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ዕጩ መልማይ ኮሚቴ ሰየሙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ስምንት አባላት ያሉት የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ዕጩ መልማይ ኮሚቴ ሰየሙ

ሰኞ ጥቅምት 26 / 2016 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ስምንት አባላት ያሉት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ዕጩ መልማይ ኮሚቴ ሰይመዋል። የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 102 እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ 1133/2011 አንቀፅ 5/1 ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዕጩ የስራ አመራር ቦርድ አባላት የሚመለምል ገለልተኛ ኮሚቴ እንደሚሰይሙ ይደነግጋል። በዚሁ መሰረት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የተሰየሙ የዕጩ ሰብሳቢ መልማይ ኮሚቴ አባላት፡- 1.  ቀሲስ ታጋይ ታደለ…………….. ሰብሳቢ 2.  ተከተል ዮሐንስ (ፕ/ር) ………….አባል 3.  ባዩህ በዛብህ…………. አባል 4.  ዮሐንስ በንቲ (ዶ/ር) …………. አባል 5.  ካሳሁን ፎሎ…………. አባል 6.  ርግበ ገብረሃዋርያ…………. አባል 7.  እንግዳዬ እሸቴ…………. አባል 8.  መላኩ እዘዘው (ኢ/ር) ………….…
ተጨማሪ ያንብቡ
“የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን የሰሞኑ ሪፖርት በትክክለኛ መረጃ ላይ ያልተመሰረተ ነው” ሲል የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ወቀሰ።

“የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን የሰሞኑ ሪፖርት በትክክለኛ መረጃ ላይ ያልተመሰረተ ነው” ሲል የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ወቀሰ።

የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሰሞኑን ያወጣው መግለጫ በትክክለኛ መረጃ ላይ ያልተመሰረተና ሚዛናዊነት የጎደለው ነው ሲሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ለገሰ ቱሉ ተናግረዋል፡፡ሚኒስትሩ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ከቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ባለፉት ጊዜያት ያከናወናቸውን ዋና ዋና ተግባራት መገምገሙን በተመለከተ  በሰጡት መግለጫ መንግስት ዜጎች ወደ መበደበኛ ኑሯቸው እንዲመለሱና መሰረታዊ መብቶቻቸው በተሻለ ሁኔታ እንዲጠበቁ በአማራ ክልል የሕግ ማስከበር ተግባራትን ሰርቷል ብለዋል፡፡መንግስት በኢትዮጵያ ነጻና ገለልተኛ ተቋማት እንዲገነቡ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ መሆኑንንና ለዚህም ማሳያ አንዱ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን አንዱ መሆኑ የተናገሩት ሚኒስትሩ ነጻና ገለልተኛ መሆን ግን ከአስፈጻሚ አካላት ብቻ ሳይሆን ከባዕዳንና ከሌሎች የውስጥ ሰርጎ ገቦች ሊሆን ይገባል ሲሉ በመግለጫቸው አንስተዋል፡፡ሚኒስትሩ…
ተጨማሪ ያንብቡ
“በደራ 3 አብያተክርስቲያናት ተቃጥለዋል ከ10 በላይ ካህናት ተገለዋል” ማኅበረቅዱሳን

“በደራ 3 አብያተክርስቲያናት ተቃጥለዋል ከ10 በላይ ካህናት ተገለዋል” ማኅበረቅዱሳን

በሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት በሚገኘው ደራ ወረዳ በታጠቁ ኃይሎች በደረሰ ጥቃት  3 አብያተ ክርስቲያናት መቃጠላቸው እና  ከ10 በላይ አገልጋይ ካህናት መገደላቸው ተገልጿል።ታጣቂዎቹ ባደረሱት ጥቃት ከ400 በላይ  መኖሪያ ቤቶች መቃጠላቸው ተገልጿል።ከደረሰው ጥቃት በኃላ  ከ8 ወረዳዎች  በርካታ ዜጎች  ወደ አጎራባች ከተሞች ተሰደዋል፡፡ችግሩን ለመፍታት የሚመለከተው አካል ምንም አይነት ጥረት እያደረገ ባለመሆኑ የምእመናኑ የመኖር ህልውና በአደጋ ውስጥ እንደሚገኝ ለከባድ እንግልትም መዳረጋቸው ማኅበረ ቅዱሳን አስታውቋል።በሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት በሚገኘው ደራ ወረዳ ታጠቁ ኃይሎች  በእምነቱ ተከታዮች ላይ ባነጣጠረ መልኩ በተፈጸመው ጥቃት በተለይም በገጠሩ ክፍል የሚገኙ አብዛኞቹ አብያተክርስቲያናት መዘጋጀታቸውን እና በደረሰው ጉዳት ቤተክርስቲያን አገልግሎት መስጠት መቆሙን  ማኅበረ ቅዱሳን ገልጿል።
ተጨማሪ ያንብቡ
ሸገር ዳቦ የምርት ስርጭቱን ከፊታችን አርብ ጀምሮ ዳግም እንደሚጀምር ተነገረ።

ሸገር ዳቦ የምርት ስርጭቱን ከፊታችን አርብ ጀምሮ ዳግም እንደሚጀምር ተነገረ።

ማክሰኞ ጥቅምት 20 ቀን 2016 በተለያዩ ምክንያቶች ተቋርጦ የነበረው ሸገር ዳቦ የምርት ስርጭት ከፊታችን አርብ ጥቅምት 23/2016 ጀምሮ ዳግም እንደሚጀምር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ አስታውቋል፡፡ በቢሮው የንግድ እና ግብይት ዘርፍ ም/ ቢሮ ኃላፊ መስፍን አሰፋ፤ የሸገር ዳቦ የምርት ስርጭት የፊታችን አርብ ዳግም እንደሚጀምር ተናግረዋል፡፡ በዚህም መሰረት የአንድ ዳቦ ዋጋ 5፡00 ብር መሆኑን የገለጹት ም/ቢሮ ኃላፊው፤ በአቅርቦት ረገድም በኹሉም አካባቢ ተደራሽ ለማድረግ የሚሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ በቀን ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ዳቦ በላይ የሚያመርተው ድርጅቱ በተለይ ከስንዴ አቅርቦትና ግዢ ጋር ተያይዞ በተፈጠረ ክፍተት ምርቱ በመዲናዋ ማሰራጨት ካቆመ ከስድስት ወራት በላይ ማስቆጠሩ ይታወቃል።
ተጨማሪ ያንብቡ