አዲስ ዜና

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ኦፊሰር አቶ በቴ ኡርጌሳ በ100 ሺ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ ፍርድ ቤት ወሰነ::

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ኦፊሰር አቶ በቴ ኡርጌሳ በ100 ሺ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ ፍርድ ቤት ወሰነ::

27/06/2016 የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ኦፊሰር አቶ በቴ ኡርጌሳ፤ 100 ሺህ ብር የዋስትና ገንዝብ በማስያዝ ጉዳያቸውን በውጭ እንዲከታተሉ በፍርድ ቤት ተወሰነላቸው። “ሁከት እና ብጥብጥ በማነሳሳት” ወንጀል ተጠርጥረው ላለፉት 13 ቀናት በእስር ላይ የቆዩት አቶ በቴ ዛሬ የአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት ቀርበው ነበር፡፡ በዛሬው ችሎት ላይ ፖሊስ “ምርመራዬን አልጨረስኩም” በሚል ተጨማሪ 11 የምርመራ ቀናትን ጠይቋል።የአቶ በቴን የስልክ የምርመራ ውጤት ለመቀበል ለኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በተደጋጋሚ ጥያቄ ባቀርብም   እስካሁን ውጤቱን ለመቀበል አልቻልኩም ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪም የሰው ማስረጃ ለማሰባሰብ ተጨማሪ ቀናት እንደሚያስፈልጓቸው አስረድተዋል።  የአቶ በቴ ጠበቃ  አቶ ቦና ያዘው፤ በተጠርጣሪው ስልክ ላይ “ምርመራ…
ተጨማሪ ያንብቡ
አዳማ ከተማ የ9ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም አሸኛፊ ሁና ተመረጠች::

አዳማ ከተማ የ9ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም አሸኛፊ ሁና ተመረጠች::

 የካቲት 15/2016 ዘንድሮ የዘጠነኛው የኢትዮጵያ የከተሞች ፎረም ተረኛ አዘጋጅ  የወላይታ ሶዶ ከተማ ነበረች፡፡ፎረሙን የኢትዮጵያ ከተሞች የትብብር መድረክ፣ የኢፌዲሪ ከተማና መሰረተ ልማት ሚስቴርና የወላይታ ሶዶ ከተማ አሰተዳደር በጋራ አሰናድተውታል፡፡ ለሰባት ተከታታይ ቀናት በቆየው በዚህ ዓውደ ርዕይ ላይ 124 ከተሞች በከተማ ልማት ዘርፍ ያከናወኗቸውን ተግባራት ለጎብኝዎች አስተዋውቀዋል፡፡ዓውደ ርዕዩ ከተሞች ልምድ የተለዋወጡበት፣ ሃሳባቸውን ያጋሩበት፣ የዕውቀት ሽግግር ያደረጉበት  መድረክ ነበር፡፡ “የዘመኑ ከተሞች ለኢትዮጵያ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው ዓውደ ርዕይ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር  አቶ ተመስገን ጥሩነህ አማካኝነት ተከፍቶ ለአንድ  ሣምንት ቆይታ አድርጎ ተጠናቋል፡፡ ከተሞች ካቀረቡት ዓውደ ርዕይ ጎን ለጎን በከተማ ልማት ዘርፍ በተለያዩ ጽንሰ ሃሳቦች ዙሪያ  የፓናል ውይይቶች የተካሄዱ ሲሆን…
ተጨማሪ ያንብቡ
ህወሓት ኬሪያ ኢብራሂም እና ሙሉ ገብረ እግዚብሔርን ከፓርቲ አባልነታቸው አሰናበተ

ህወሓት ኬሪያ ኢብራሂም እና ሙሉ ገብረ እግዚብሔርን ከፓርቲ አባልነታቸው አሰናበተ

የካቲት 15/2016 የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ትላንት ሐሙስ የካቲት 15፤ 2016 ባደረገው ስብሰባ ከከፍተኛ አመራሮቹ ውስጥ፤ ኬሪያ ኢብራሂም እና ሙሉ ገብረ እግዚብሔርን ከማዕከላዊ ኮሚቴ እና ከፓርቲ አባልነታቸው ማሰናበቱን አስታወቀ። ዶ/ር አዲስ አለም ባሌማ እና ዶ/ር አብርሃ ተከስተ በፓርቲው የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲቀጥሉ ወስኗል፡፡ ህወሓት በጦርነቱ ወቅት “በጠላት እጅ ወድቀው ነበር” ያላቸውን የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን  ያሰናበተው አስቀድሞ የነበሩትን ሁኔታዎች በመገምገም እና የፓርቲውን ህገ ደንብ በመከተል መሆኑን ዛሬ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል። በዚህም መሰረት “እጃቸውን ለጠላት በመስጠት” እና “ምስጢር አሳልፈው በመስጠት” የተገመገሙት የቀድሞው የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም እና የትራንስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሙሉ ገብረ እግዚብሔር፤ ከማዕከላዊ…
ተጨማሪ ያንብቡ
“ዝክረ የኢትዮጵያ አብዮት ”በፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ

“ዝክረ የኢትዮጵያ አብዮት ”በፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ

እታገኘሁ መኮነን የካቲት  13/2016 የኢትዮጵያ አብዮት እነሆ ሃምሳ አመት ደፈነ፡፡ በዚህ ሃምሳ ዓመት ውስጥ በኢትዮጵያ  ለታዩ የፖለቲካ ከፍታና ዝቅታዎች  አብዮቱ ምን አበረከተ ? ሲል ለመጠየቅ እና ለማወያየት መዘጋጀቱን ፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ (FSS) ባሳለፍነው ሰኞ የካቲት 11/2016 ለመገናኛ ብዙሃን  በሰጠው መግለጫ ይፋ አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ አብዮት ‹‹ከየካቲት እስከ የካቲት›› በሚል ርዕስ  በስድስት ወሳኝ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር የውይይት መድረክ ከያዝነው የካቲት ወር ማብቂያ  ጀምሮ በየሁለት ወሩ  ለማካሄድ መዘጋጀታቸውን የተናገሩት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ የራስ ወርቅ አድማሴ (ዶር ) ናቸው፡፡የአብዮቱ መሰረታዊ ጥያቄ መልስ አግኝቷል ወይስ አላገኘም  ? አገሪቱንስ ወዴት አቅጣጫ ወሰዷት ? የመሬት ለአራሹ አዋጅ የኢትዮጵያ አርሶ አደሮችን…
ተጨማሪ ያንብቡ
“ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸው ዜጎች የሥነ ልቦና አገልግሎት፣ የሕግና የመልሶ ማቋቋም ድጋፍ እየተደረገላቸው አይደለም፡፡” ኢሰመኮ

“ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸው ዜጎች የሥነ ልቦና አገልግሎት፣ የሕግና የመልሶ ማቋቋም ድጋፍ እየተደረገላቸው አይደለም፡፡” ኢሰመኮ

የካቲት 13/2016 እታገኘሁ መኮነን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በትግራይ ክልል አምስት ዞኖች አስተዳደሮች ውሰጥ ሰብዓዊ መብትና ሰብዓዊ ቀውስን በተመለከተ አካሄድኩት ያለውን የምርመራ ሪፖርት ማክሰኞ የካቲት 12 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ በሪፖርቱም በትግራይ ክልል በተለያየ ጊዜ ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸው ዜጎች የሥነ ልቦና አገልግሎት፣ የሕግና የመልሶ ማቋቋም ድጋፍ እየተደረገላቸው አለመሆኑን አስታውቋል፡፡ አብዛኞቹ  ጥቃቶች የተፈጸሙት ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ ነው ያለው ኮሚሽኑ በተለይ ደግሞ ጥቃቱ ተባብሶ የሚታየው በኤርትራና በአማራ ኃይሎች ቁጥጥር ስር በሚገኙ  አካባቢዎች እንደሆነ ተገልጽዋል፡፡ ጾታዊ ጥቃት የሚደርስባቸው ሴቶች በከፍተኛ ሁኔታ መገለል ስሚደርስባቸው ከማህበረሰቡ እየራቁ እና ለስነልቦና ጉዳት እየተዳረጉም ነው ሲል ኮሚሽኑ የችግሩን ስፋት ትናንት ባወጣው ሪፖርቱ…
ተጨማሪ ያንብቡ
በሶማሌ ክልል የተገነባው ጎዴኡጋዝ አየር ማረፊያ ዛሬ ተመረቀ

በሶማሌ ክልል የተገነባው ጎዴኡጋዝ አየር ማረፊያ ዛሬ ተመረቀ

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፣ በሶማሌ ክልል ጎዴ ከተማ አዲስ የተገነባውን ጎዴ ኡጋዝ ሚራድ አውሮፕላን ማረፊያ ዛሬ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት ማድረጋቸውን የክልሉ ኮምንኬሽን አስታውቋል። አውሮፕላን ማረፊያው በአንድ ጊዜ አራት ቦይንግ 737 የመንገደኞች አውሮፕላኖችን ማስተናገድ እንደሚችል ቢሮው ገልጧል። ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሠፈሩት መልዕክት፣ አዲሱ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናልና አውሮፕላን ማረፊያ ፍትሐሃዊ የልማት ተደራሽነትን የሚያረጋግጥ መሆኑን  ተናግረዋል፡፡ የአውሮፕላን ማረፊያውን ተርሚናል ግንባታ ያከናወነው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ነው።
ተጨማሪ ያንብቡ
በአማራ ክልል መርዓዊ አካባቢ ንጹሀን ዜጎች “ግድያ” በገለልተኛ አካል ይመርመር ሲል የአሜሪካ መንግስት ጠየቀ

በአማራ ክልል መርዓዊ አካባቢ ንጹሀን ዜጎች “ግድያ” በገለልተኛ አካል ይመርመር ሲል የአሜሪካ መንግስት ጠየቀ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኢርቪን ማሲንጋ የአሜሪካ መንግስት በአማራ ክልል መርዓዊ አካባቢ ንጹሀን ተገድለዋል መባሉ እንዳሳሰበው አስታወቁ። የአሜሪካ መንግስት በአማራ ክልል ተፈጽሟል የተባለው የንጹሀን ግድያ በገለልተኛ አካላት እንዲመረመር እንዲሁም ለሰብዓዊ መብት መረጃ ስብሰባ ያልተገደበ ስርዓት እንዲኖር አጽንዖት ሰጥቷል። በአማራ፣ ኦሮሚያ እና ሌሎችም የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመንግስት ኃይሎች እና ታጣቂዎች የሚፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን ለመግታት "ከግጭት ይልቅ መነጋገር" የተሻለ አማራጭ ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር የተናገሩት።
ተጨማሪ ያንብቡ
የኢትዮጵያ  የሃይማኖት  ተቋማት ጉባኤ መንግስት ግብረ ሰዶማዊነትን መብትን የሚፈቅድ  የሳሞአ ስምምነት መፈረሙን እቃወማለው አለ

የኢትዮጵያ  የሃይማኖት  ተቋማት ጉባኤ መንግስት ግብረ ሰዶማዊነትን መብትን የሚፈቅድ  የሳሞአ ስምምነት መፈረሙን እቃወማለው አለ

የካቲት 1/2016 የኢትዮጵያ  የሃይማኖት  ተቋማት ጉባኤ  ዛሬ በሰጠው መግለጫ  በአውሮጳፓ ህብረት እና በአፍሪካ ፣በካሪቢያንና በፓስፊክ  ሀገራት ለ 20 አመታት እንዲዘልቅ ታሳቢ ተደርጎ የተከናወነው  የንግድና የኢኮኖሚ ትብብር  በውስጡ  ከኢትዮጵያ ህዝብ  የሃይማኖትና የባህል እሴቶች ጋር የሚፃረሩ ፅንሰ ሀሳቦችና  ትርጎሞች  ስላለው የሳሞአ ስምምነትን ያደረገው  የኢትዮጵያ መንግስት ስምምነቱን እንዲሰረዝ  ጠይቋል። ጉበኤው በስምምነቱ  ግብረሰዶም  ፣ ፆታ መቀየር ፣ ውርጃ  እና ሁሉና ዓቀፍ  ግልሙትናን  ህጋዊ  የማድረግ አንቀጾች ተካተዋል ብሏል። በተጨማሪ   እጅግ አደገኛ  ይዘት ያለው  ለአህጉሪቱ ልጆችና ታዳጊዎች ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርት  አስገዳጅ በሆነ መንገድ  እንዲሰጥ የሚል ነጥብ ተካቷል ይሄም የኢትዮጰያን ባህል ክፉኛ የሚጎዳ ነው ብሏል።
ተጨማሪ ያንብቡ
አቶ ተመስገን ጥሩነህ የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሁነው ተሾሙ። አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነዋል።

አቶ ተመስገን ጥሩነህ የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሁነው ተሾሙ። አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነዋል።

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ ስብሰባ የአቶ ተመስገን ጥሩነህን ም/ጠ/ሚኒስትርነት እና የአምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሹመት አጽድቋል። ጠ/ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የአቶ ተመስገን ጥሩነህን እና የአምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴን የሥራ ልምድ ዘርዝረው ለምክር ቤቱ ባቀረቡት መሰረት ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ሹመቶቹን አጽድቋል።
ተጨማሪ ያንብቡ
”በመቶ የሚቆጠሩ እስረኞች ብቻ ናቸው ያሉት ” ጠ/ሚኒስትር ዐብይ አህመድ

”በመቶ የሚቆጠሩ እስረኞች ብቻ ናቸው ያሉት ” ጠ/ሚኒስትር ዐብይ አህመድ

ትናንት በህዝብተወካዮች ም/ቤት  የኢትዮጵያን የፀጥታ ሁኔታበሚመለከት ማብራሪያ ያቀረቡት ጠ/ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የኢትዮጵያን ሰላም የሚያውኩት አካላት  የፖለቲካ ፍላጎት የማሳኪያ ልምምድ የሌላቸው ናቸው ሲሉ የተቹ ሲሆን ከሸኔ ጋር በታንዛንያ የተደረገው ድርድር ያለ ውጤት በመጠናቀቁ ምክንያት ምንም ለህዝብ ይፋ ማድረግ የተቻለ ነገር የለም ብለዋል፡፡ በአማራ ክልል የሚታየውን አለመረጋጋት በተመለከተ የአማራ ሕዝብ መሠረታዊ ጥያቄዎች ልማት፣ የሕገ መንግሥት ማሻሻያ እና የወሰን ጉዳዮች ናቸው ያሉ ሲሆን ከሰላም ማስከበር ጋር በተያያዘ ግን መንግሥት በቀጣይነት ሕግ የማስከበር ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል። እጃችሁን አጣጥፋችሁ ተቀመጡ የሚለውን ጉዳይ አንስማማም አንቀበልም አናደርግም። መንግሥት ነን አቅም በፈቀደ መጠን ሕግ ለማስከበር እንሰራለን  ሲሉ አክለዋል። "ሕግ ለማስከበር ስንሰራ በየአንዳንዷ ሰከንድ…
ተጨማሪ ያንብቡ