የአገራዊ ምክክር ሒደቱ በትግራይ ክልል እንዲጀመር ጥያቄ ቀረበ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ያቀረበውን የሥራ አፈጻጸምና ቀጣይ አቅጣጫ በማስመልከት ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ውይይት አድርጓል፡፡ በውይይቱም የምክር ቤቱ አባላት በትግራይ ክልል የሃገራዊ ምክክር ሒደት እንዲጀመር ጠይቀዋል፡፡ ለምክር ቤቱ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽንን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕሮፌሰር)፣ ከትግራይ ክልል ውጪ የአማራ ክልልን ጨምሮ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተባባሪዎች ሥልጠና መሰጠቱን ገልጸዋል፡፡ ነገር ግን የተሳታፊ ልየታና መረጣ ባሉት ነባራዊ ሁኔታዎች ምክንያት በአማራና በትግራይ ክልሎች አለመጀመሩን ተናግረዋል፡፡ በአማራ ክልል ባለው ግት ምክንያት 800 ያህል ለሚሆኑ ተባባሪዎች ሥልጠና ለመስጠት ታቅዶ ለ200 ያህሉ ብቻ መሰጠቱን ጠቁመዋል፡፡ በሌላ በኩል ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል ምንም ዓይነት ሥራዎችን…
