ሰኞ ጥቅምት 26 / 2016
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ስምንት አባላት ያሉት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ዕጩ መልማይ ኮሚቴ ሰይመዋል።
የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 102 እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ 1133/2011 አንቀፅ 5/1 ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዕጩ የስራ አመራር ቦርድ አባላት የሚመለምል ገለልተኛ ኮሚቴ እንደሚሰይሙ ይደነግጋል።
በዚሁ መሰረት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የተሰየሙ የዕጩ ሰብሳቢ መልማይ ኮሚቴ አባላት፡-
1. ቀሲስ ታጋይ ታደለ…………….. ሰብሳቢ
2. ተከተል ዮሐንስ (ፕ/ር) ………….አባል
3. ባዩህ በዛብህ…………. አባል
4. ዮሐንስ በንቲ (ዶ/ር) …………. አባል
5. ካሳሁን ፎሎ…………. አባል
6. ርግበ ገብረሃዋርያ…………. አባል
7. እንግዳዬ እሸቴ…………. አባል
8. መላኩ እዘዘው (ኢ/ር) …………. አባል ናቸው።
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ዕጩ መልማይ ኮሚቴው ወደ ሥራ የገባ ሲሆን፤ በቅርቡም ጥቆማ መቀበል ይጀምራል መባሉን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
