ቀይባህር

ሌሎች አካላት ቀጠናውን ለማተራመስ ሲንቀሳቀሱ ኢትዮጵያ ቆማ እንደማትመለከት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ

ሌሎች አካላት ቀጠናውን ለማተራመስ ሲንቀሳቀሱ ኢትዮጵያ ቆማ እንደማትመለከት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ማምሻውን ባወጣው ባወጣው መግለጫው ሌሎች አካላት ቀጠናውን ለማተራመስ ሲንቀሳቀሱ ኢትዮጵያ ቆማ እንደማትመለከት አስታውቋል። መግለጫው የወጣው በትናንትናው እለት የግብፅ የጦር አውሮፕላኖች ወደ ሶማልያ መዲና ሞቃዲሾ ቀሳቁስ እና ወታደሮችን ማጓጓዛቸው ይፋ ከሆነ በኋላ ነው። "ኢትዮጵያ ብሄራዊ ፀጥታዋን ሊያውኩ የሚችሉ በቀጠናው እየተከናወኑ ያሉ ድርጊቶችን በንቃት እየተከታተለች ነው" ያለው መግለጫው የሶማልያ መንግስት ከውጫዊ ሀይሎች ጋር በማበር ቀጠናው ላይ ውጥረት እየፈጠረ ነው ብሎ ከሷል። መግለጫው አክሎም "ለአጭር ግዜ እና እርባና ቢስ ጥቅም ብለው አካባቢው ላይ ውጥረት የሚነዙ ሀይሎች ለድርጊታቸው ተጠያቂ ይሆናሉ" ብሏል። ይሁንና መግለጫው በትናንትናው እለት አውሮፕላኖችን ወደ ሶማልያ ያሰማራችውን ግብፅን በስም አልጠቀሰም። የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና…
ተጨማሪ ያንብቡ
በቱርክ የተገናኙት ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ አለመግባባቶችን በሰላም እንደሚፈቱ ገለጹ

በቱርክ የተገናኙት ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ አለመግባባቶችን በሰላም እንደሚፈቱ ገለጹ

ራሷን በነጻ አገርነት ካወጀችው ሶማሊላንድ ጋር ኢትዮጵያ  ከስድስት ወራት በፊት  የባህር በር መግባቢያ ስምምነት መፈራረሟን ተከትሎ ነበር ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ  ውዝግብ ውስጥ የገቡት፡፡ በዚህም ምክንያት ሰኔ 24/ 2016 ዓ.ም በቱርክ ጋባዥነት ለመጀመሪያ ጊዜ በመሃላቸው በተፈጠረው አለመግባባት ዙሪያ ለመነጋገር  ወደ ቱርክ   አንካራ ያቀኑት ኢትዮጵያና ሶማሊያ  በመካከላቸው ያሉ አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልፀዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታየ አጽቀስላሴ እና የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አህመድ ሞሊም ከውይይታቸው በኋላ በጋራ ባወጡት መግለጫ ነው ይህንን ያስታወቁት። በቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃካን ፊዳን አመቻችነት የተገናኙት የሁለቱ ሃገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች  ያላቸውን ልዩነቶች ለሁለቱም ተቀባይነት…
ተጨማሪ ያንብቡ
የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሃመድ ለይፋዊ ጉብኝት ትናንት ኳታር ገብተዋል።

የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሃመድ ለይፋዊ ጉብኝት ትናንት ኳታር ገብተዋል።

14/05/2016 ፕሬዝዳንት ሞሃመድ ወደ ዶሃ የተጓዙት፣ በቅርብ ጊዜያት በሱማሊያ በተፈጠሩ እንዳንድ ክስተቶች ዙሪያ ከአገሪቱ መሪዎች ጋር ለመወያየት እንደኾነ የፕሬዝዳንቱ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር በተፈራረመችው የባሕር በር የመግባቢያ ስምምነት ሳቢያ በሱማሊያና ኢትዮጵያ መካከል ውጥረት ከተፈጠረ ወዲህ፣ ፕሬዝዳንት ሞሃመድ በኤርትራና ግብጽ ይፋዊ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወሳል። ሶማሊላንድ ግን ከኢትዮጵያ ጋር ከተፈራረመችው የባሕር በር የመግባቢያ ስምምነት ጋር በተያያዘ ማናቸውንም የውጭ ጣልቃ ገብነት እንደምትቃወም አስታውቃለች። ሶማሊላንድ በውጭ ጉዳይ ሚንስቴሯ በኩል ትናንት ባወጣችው መግለጫ፣ ግብጽ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቷን እንደ ሱዳን፣ ሊቢያና ጋዛ በመሳሰሉ ግጭቶች ባሉባቸው ጎረቤቶቿ ላይ ብታውለው ይሻላታል ብላለች። ቀጠናዊ ጉዳዮችን በንግግርና ትብብር ለመፍታት ቁርጠኛ መሆኗን የጠቀሰችው ሶማሊላንድ፣ በቀጠናው ሰላምና…
ተጨማሪ ያንብቡ
”የሶማሊያ ሉዓላዊ ግዛትን የሚመለከት ማንኛውም ስምምነት የሃገሪቱን መንግስት ይሁንታ ሊያገኝ ይገባል” ኢጋድ

”የሶማሊያ ሉዓላዊ ግዛትን የሚመለከት ማንኛውም ስምምነት የሃገሪቱን መንግስት ይሁንታ ሊያገኝ ይገባል” ኢጋድ

በእታገኘሁ መኮነን 09/05/2016 የቀጠናው ሃገራት እና የቀጠናውን ጉዳይ በትኩረት የሚከታተሉ ሁሉ በጉጉት ሲጠብቁት የነበረው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ) አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ ሐሙስ ጥር 9፤ 2016 በኡጋንዳ ኢንተቤ ከተማ ተካሂዷል፡፡ መሪዎቹ በጉባኤው ማጠናቀቂያ ላይ ባወጡት መግለጫ ''የሶማሊያ ሉዓላዊ ግዛትን የሚመለከት ማንኛውም ስምምነት የሀገሪቱን መንግስት ይሁንታ ሊያገኝ ይገባል ''  ብለዋል ፡፡መሪዎቹ ማንኛውም ግንኙነት የሶማሊያን ''ሉዓላዊነት፣ አንድነት እና የግዛት አንድነት ያከበረ ሊሆን እንደሚገባም'' አሳስበዋል። በጉባኤው ላይ የአስተናጋጇ ሀገር ኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ፣  የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሐመድ ፣የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማህማት፣ የኢጋድ ዋና ጸሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ፣ የሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ…
ተጨማሪ ያንብቡ
የአሜሪካው የአፍሪቃ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ  ማይክ ሐመር  ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ አሳውቋል፡፡

የአሜሪካው የአፍሪቃ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ  ማይክ ሐመር  ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ አሳውቋል፡፡

09/05/2016 የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪቃ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር  ወደ ካምፓላ እና አዲስ አበባ ይጓዛሉ ብሏል የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በመግለጫው ። አምባሳደር ሐመር በካምፓላ ፤ በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል ባለው ወቅታዊ ሁኔታ እና በሱዳን ላይ በሚያተኩረው 42ኛው የምስራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የመሪዎች ጉባኤ ላይ ይሳተፋሉ ተብሏል። አምባሳደር ሐመር ከካምፓላ በኋላ ወደ አዲስ አበባ እንደሚያቀኑ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ ላይ ገልጿል።በኡጋንዳ መዲና ዛሬ የሚካሄደው የኢጋድ ስብሰባ ከያዛቸው ሁለት መወያያ ርዕሶች አንደኛው በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል የተፈጠረው ውጥረት ነው።ኢጋድ ይህን በተመለከተ ውይይት ለማድረግ ስብሰባ መጥራቱን ያወደሰችው አሜሪካ ተወካይዋ አምባሳደር ሐመር…
ተጨማሪ ያንብቡ
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የአብሮነት ትስስራቸው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ከሚያሳድሩ ተጨማሪ እርምጃዎች እና መግለጫዎች እንዲቆጠቡ የአፍሪካ ህብረት አሳሰበ

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የአብሮነት ትስስራቸው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ከሚያሳድሩ ተጨማሪ እርምጃዎች እና መግለጫዎች እንዲቆጠቡ የአፍሪካ ህብረት አሳሰበ

09/05/2016 የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና የፀጥታው ምክር ቤት ትናንት ጥር 8/2016 ዓም  በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል ስላለው ሁኔታ ለመመካከር ስብሰባ አካሂዶ ነበር። የስብሰባው መርሐ ግብር ቀደም ተብሎ የተያዘ አልነበረም፡፡በኢትዮጵያ እና በሶማሌላንድ መካከል የመግባቢያ ስምምነት ከተፈረመ በኋላ በሶማሊያ እና ኢትዮበሁለቱ ሃገራት  መካከል የተፈጠረው አለመግባባት እየተባባሰ በመምጣቱ ምክንያት ስብሰባውን ማድረግ እንዳስፈለገ ምክርቤቱ ተናግሯል፡፡ የሶማሊያ ባለስልጣናት የሀገራቸውን ዳር ድንበር ለመጠበቅ ወደ ጦርነት ለመግባት ያላቸውን ቁርጠኝነት ካስታወቁ በኋላ ሶማሊያ በጉዳዩ ላይ ስብሰባ እንዲጠሩ ለአፍሪካ ህብረት እና ለተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት (UNSC) ጥያቄ መላኳ ተሰምቶ ነበር። ሁኔታው እየተባባሰ በመምጣቱ ሀገራቱ  ወደ ግጭት ሊያመሩ ይችላሉ ከሚለው ስጋት በተጨማሪ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው…
ተጨማሪ ያንብቡ
ሱዳን ከኢጋድ አባልነቷ ለቀቀች

ሱዳን ከኢጋድ አባልነቷ ለቀቀች

ሱዳን፣ ኢጋድ በውስጥ ጉዳዬ ጣልቃ ገብቷል በማለት ከድርጅቱ ጋር ያላትን ግንኙነት ማቋረጧን ዛሬ አስታውቃለች። የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር የኢጋድ የወቅቱ ሊቀመንበር ለሆነችው ጅቡቲ አቻቸው በጻፉት ደብዳቤ፣ ይህንኑ ውሳኔ አሳውቀዋል። ሱዳን ከኢጋድ ጋር ግንኙነቷን ያቋረጠችው፣ በመጭው ሐሙስ ኡጋንዳ ላይ የተጠራው የኢጋድ መሪዎች አስቸኳይ ጉባዔ ወታደራዊውን መንግሥት ሳያማክር የሱዳኑን ጦርነት አጀንዳው ማድረጉንና የፈጥኖ ደራሹን ኃይል እንዲገኙ መጋበዛቸውን በመቃወም ነው። የሱዳኑ ወታደራዊ መሪ ጀኔራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን በኢጋድ ጉባኤ ላይ እንደማይገኙ ከትናንት ወዲያ ማሳወቃቸው ይታወሳል። ኢጋድ አስቸኳዩን የመሪዎች ጉባኤ የጠራው፣ በሱዳኑ ጦርነት ዙሪያ ለመወያየትና የኢትዮጵያና ሱማሊያ ዲፕሎማሲያዊ ውጥረትን ለማብረድ ነበር።
ተጨማሪ ያንብቡ
በሶማሊላንድ ሃርጌሳ ጸረ ኢትዮጵያውያን እንቅስቃሴዎች መጀመራቸው ተነገረ።

በሶማሊላንድ ሃርጌሳ ጸረ ኢትዮጵያውያን እንቅስቃሴዎች መጀመራቸው ተነገረ።

01/05/2016 ከኢትዮጵያ ጋር የወደብ ኪራይ ስምምነት ውል የገባችው ሶማሊላንድ ስምምነቱን በሚቃወሙ ሰዎች በሶማሊኛ ቋንቋ “ኢትዮጵያዊ ላይ በተገኘበት እርምጃ ይወሰድበት” የሚል በራሪ ጽሑፍ በሐርጌሳ ከተማ እየተበተነ መሆኑ ተነግሯል። በዚህም ምክንያት በሶማሊላንድ ለሚገኙ ከ 40 ሺ በላይ ለሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በጣም አሳሳቢ ወቅት ሆኗል። በተለይም የኦሮሞ ተወላጆች በሚኖሩበት አካባቢ ላይ ትኩረት በማድረግ በሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ለማድረስ፣ ንብረት ለመዝረፍ፣ እና ቤታቸውን በእሳት ለማቃጠል ሙከራ ተደርጓል  ተብሏል። በሶማሊላንድ ሁለተኛ ትልቋ ከተማ በሆነችው በቦርኦ ከተማ በተካሄዱ የተቃውሞ ሰልፎች በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ ጉዳት መድረሱን እና ንብረታቸው መዘረፉ ተነግሯል። በሶማሊላንድ የስደተኞች ተወካይ እንደሚሉት ስደተኛ ነዋሪዎች ስጋታቸውን ለሶማሊላንድ ባለስልጣናት ካሳወቁ በኋላ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች…
ተጨማሪ ያንብቡ
በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና የበረሃ አንበጣና ድንበር ተሻጋሪ ተባዮች ስጋት ናቸው ተብሏል።

በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና የበረሃ አንበጣና ድንበር ተሻጋሪ ተባዮች ስጋት ናቸው ተብሏል።

ይህ ይፋ የተደረገው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የአየር ንብረት ትንበያ እና ትግበራ ማዕከል ICPAC ከኢጋድ አባለ ሀገራት ለተወጣጡ ጋዜጠኞች በሰጠው ስልጠና ላይ ነው። ስልጠናው በዋናነት የበረሃ አንበጣና በሌሎች ድንበር ተሻጋሪ ፀረ ሰብል ተባዮች ላይ ያተኮረ ነው። በተለይ  ባለፉት አራት አመታት በቀጠናው ክፉኛ የአንበጣ መንጋ ተከስቶ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የማዕከሉ ሪፓርት አመላክቷል። በጎረቤት ኬንያ ምዕራባዊ ክፍል በተገባደደው የፈረንጆቹ 2023 ብቻ 5.5 ትሪሊዮን ዶላር የሚገመት እህል በወፎች ወድሟል። ይህም በቶን ሲሰላ 60ቶን ገደማ ነው ተብሏል። በወፎች ከሚጠቁ የሰብል አይነቶች ውስጥ ማሽላ፣ስንዴ፣ሩዝ ጤፍ እና ገብስ በግባር ቀደምትነት ይጠቀሳሉ።የሙቀት መጠን በከፍተኛ ደረጃ መጨመር ለተባዮች መፈልፈል እና መራባት…
ተጨማሪ ያንብቡ

በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና የበረሃ አንበጣና ድንበር ተሻጋሪ ተባዮች ስጋት ናቸው ተብሏል።

03/2016 በተለይ ባለፉት አራት አመታት በቀጠናው ክፉኛ የአንበጣ መንጋ ተከስቶ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የማዕከሉ ሪፓርት አመላክቷል። በጎረቤት ኬንያ ምዕራባዊ ክፍል በተገባደደው የፈረንጆቹ 2023 ብቻ 5.5 ትሪሊዮን ዶላር የሚገመት እህል በወፎች ወድሟል። ይህም በቶን ሲሰላ 60ቶን ገደማ ነው ተብሏል። ይህ ይፋ የተደረገው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የአየር ንብረት ትንበያ እና ትግበራ ማዕከል ICPAC ከኢጋድ አባለ ሀገራት ለተወጣጡ ጋዜጠኞች በሰጠው ስልጠና ላይ ነው። ስልጠናው በዋናነት የበረሃ አንበጣና በሌሎች ድንበር ተሻጋሪ ፀረ ሰብል ተባዮች ላይ ያተኮረ ነው። በወፎች ከሚጠቁ የሰብል አይነቶች ውስጥ ማሽላ፣ስንዴ፣ሩዝ ጤፍ እና ገብስ በግባር ቀደምትነት ይጠቀሳሉ።የሙቀት መጠን በከፍተኛ ደረጃ መጨመር ለተባዮች መፈልፈል እና…
ተጨማሪ ያንብቡ