አስፋውን ተሰናበትነው
በበርካቶች ዘንድ በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ "ሞቅ ደመቅ ሸብረቅ" በምትል ንግግሩ ይታወቃል፡፡ አስፋው መሸሻ፡፡ መሸሻ ይሙት የሚለው መሃላውም አይረሳም፡፡ ከአባቱ ከአቶ መሸሻ አስፋው እና ከእናቱ ከ ወ/ሮ ዘነበወርቅ አሻግሬ ሀምሌ 1959 ዓም በአዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ ‹‹ሰሜን ማዘጋጃ ችሎት ሰፈር›› በሚባለው አካባቢ የተወለደው አስፋው ለቤተሰቡ አምስተኛ ልጅ እንደሆነ ይነገራል።አባቱ ዲፕሎማት በመሆናቸው እና ለሥራ ጉዳይ ወደ ተለያዩ ክፍለ ዓለማት ይዘዋወሩ ስለነበር ትምህርቱን በኢትዮጵያ፣ታንዛንያ እና ኬንያ ተከታትሏል። አስፋው ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ ከጓደኛው ዳንኤል ግዛው ጋር በኤፍ ኤም 97.1 ላይ በጋራ "አይሬ"የተሰኘ ፕሮግራም ማዘጋጀት እና ማቅረብ ጀመረ፡፡ በአይሬ ፕሮግራሙ ተወዳጅነትን ያተረፈው አስፋው ከሃገር እስከወጣበት ጊዜ ድረስ በኤፍ ኤም 97.1…
