ከተመን በላይ ነዳጅ የሚሸጡ ነጋዴዎችን እስከ አምስት አመት እስር እና እስከ 500 ሺህ ብር የሚያስቀጣ አዋጅ ጸደቀ፡፡አዋጁ ከምክር ቤት አባላት ጠንካራ ተቃውሞ ገጥሞታል፡፡
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ጥር 1 ቀን 2017 ባካሄደው ስብሰባ መንግሥት ከተመነው የመሸጫ ዋጋ በላይ ሲሸጡ የተገኙ ነጋዴዎች ከሦስት ዓመት እስከ አምስት ዓመት የሚደርስ የእስር ቅጣት እና እስከ አምስት መቶ ሺህ ብር እንዲቀጡ የሚያደርግ አዋጅ አጽድቋል፡፡ በአዋጁ መሠረት ከመሸጫ ዋጋ በላይ በመሸጥ የሚፈጸም የመጀመሪያ ጥፋት ከሦስት መቶ ሃምሳ ሺህ እስከ አምስት መቶ ሺህ ብር ያስቀጣል።ድርጊቱ በተደጋጋሚ ከተፈጸመ ከገንዘብ ቅጣት በተጨማሪ ከሦስት ዓመት እስከ አምስት ዓመት የሚደርስ የእስር ቅጣት እንደሚኖር በአዋጁ ተደንግጓል። ድርጊቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲፈጸም ከ300 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር የሚያስቀጣ ሲሆን፣ በተደጋጋሚ ከተፈጸመ ከሦስት ዓመት እስከ አምስት ዓመት እስራት እና ከ350 ሺህ እስከ…
