አዲስ ጊዜ

230 Posts
ኢሰመኮ ዓለም አቀፍ ለጋሽ ድርጅቶች እርዳታ ለመቀጠል መወሰናቸውን አደነቀ

ኢሰመኮ ዓለም አቀፍ ለጋሽ ድርጅቶች እርዳታ ለመቀጠል መወሰናቸውን አደነቀ

ዳዊት ታደሰ የኢትዮጵያ ሰበአዊ መብቶች ኮሚሽን ህዳር 07 ቀን 2016 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ የአሜሪካ መንግስት የዓለም አቀፍ ልማት ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስ ኤድ) እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዓለም የምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ አቋርጠውት የነበረውን የምግብ እርዳታ መልሰው ለመጀመር መወሰናቸው የሚወደስ ነው ብሏል፡፡ ኢሰመኮ በመግለጫው፣ በትግራይ ክልል ከባለፈው ዓመት መጋቢት ወር ጀምሮ በኢትዮጵያ ደረጃ ደግሞ ከሰኔ ወር ጀምሮ የተቋረጠውን የምግብ እህል እርዳታ ተከትሎ ስለተፈጠረው ሁኔታ ክትትል ሲያደርግ እንደነበር ዘርዝሯል፡፡ ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ፍልሰተኞች በተለይ ደግሞ ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ ህጻናት ጋር ለመድረስ እንዲቻል አስተዳደራዊ እርምጃዎችን ጨምሮ ሌሎች የማስተባበር ስራዎች በፍጥነት እንዲከወኑ ሲወተውት መቆየቱን ያስታወሰው ኮሚሽኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት…
ተጨማሪ ያንብቡ
ዩ.ኤስ.ኤድ ያቋረጠውን ርዳታ ሊጀምር ነው

ዩ.ኤስ.ኤድ ያቋረጠውን ርዳታ ሊጀምር ነው

ዩኤስኤድ ከወራት በፊት አቋርጦት የነበረውን የምግብ እርዳታ አቅርቦት ከቀጣይ ወር ጀምሮ በመላ ኢትዮጵያ እንደሚጀምር ማስታወቁ ተዘግቧል።በኢትዮጵያ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለተጎጂዎች ተብሎ የሚቀርብ እርዳታ ላልታለመለት አላማ እየዋለ መሆኑ በመረጋገጡ የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት ዩኤስኤድ በኢትዮጵያ የሚያካሂደውን የእርዳታ አቅርቦት ማቋረጡ ይታወሳል። ዩ.ኤስ.ኤድ በመላ ሀገሪቱ ለአንድ አመት ያክል የእርዳታ ስርጭቱን በማካሄድ ለመሞከር ማቀዱን አስታውቋል ያለው የሮይተርስ ዘገባ በዚህ የሙከራ ጊዜ የምግብ እርዳታውን አቅርቦት ለሚገባቸው ተረጂዎች መዳረሱን ክትትል እንደሚያደርግ እና ምርምራ እንደሚያከናውን መግለጹን አመላክቷል። የረድኤት ድርጅቱ የምግብ አቅርቦቱን የሚጀምረው ለበርካታ ወራት ከመንግስት ጋር ዲፕሎማሲያዊ ድርድሮች ከተከናወኑ በኋላ መሆኑን የጠቆመው ዘገባው የኢትዮጵያ መንግስት እና አጋር አካላት ከእርዳታ እደላ ጋር በተያያዘ እጅግ አስፈላጊ…
ተጨማሪ ያንብቡ
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የፓርላማ ውሎ

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የፓርላማ ውሎ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባውን ህዳር 4 ቀን 2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት አካሂዶ ነበር። የምክር ቤት አባላትም ማብራሪያ ቢሰጥባቸው ያሏቸውን ጥያቄዎችና አስተያየቶች ያቀረቡ ሲሆን ጠ/ሚኒስትር ዐቢይም ምላሽ ያሉትን ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በብዙዎች ዘንድ አወዛጋቢ በተባለ በዚህ ገለፃቸው ላይ በርካታ ርዕሰ ጉዳዮች የተነሱ ሲሆን አዲስ ጊዜ ሚዲያም አንኳር ነጥቦቹን እንዲህ አሰናድታዋለች፡፡ መንግሥትን በኃይል ስለመገዳደር ለጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከቀረቡት ጥያቄዎች መካከል ትጥቅን የቀላቀሉ ትግሎችን የሚመለከተው አንደኛው ሲሆን በሀገሪቱ ውስጥ እየተካሄደ ያለውን ግጭት ወደሰላም ለማምጣት ምን እየተደረገ እንደሆነ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ጠ/ሚንስትሩ ምላሻቸውን ሲጀምሩ "ኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ መንግሥትን…
ተጨማሪ ያንብቡ
ስደተኞችን በማስጠለል ከአፍሪካ ቀዳሚ የነበረችው ኢትዮጵያ በ3ኛነት                       ተቀመጠች::

ስደተኞችን በማስጠለል ከአፍሪካ ቀዳሚ የነበረችው ኢትዮጵያ በ3ኛነት ተቀመጠች::

ለበርካታ ዓመታት በአፍሪካ በአንደኝነት ደረጃ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ስደተኛ አስጠልላ የቆየችው ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ሶስተኛዋ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ስደተኛ ተጠልሎባት የሚገኝ ሀገር ናት ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታወቀ። ሱዳንን እና ኡጋንዳን በመከተል በሶስተኝነት ስደተኞችን ያስጠለለችው ኢትዮጵያ 954ሺ ከተለያዩ ሀገራት ድንበሯን አቋርጠው የገቡ ስደተኞች እንደሚገኙባት ተቋሙ ይፋ ባደረገው መረጃ ጠቁሟል። የመንግስታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት ዩኤንኤችሲአር ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያመላክተው በኢትዮጵያ ተጠልለው ከሚገኙ ስደተኞች መካከል ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዙት ሱዳናውያን ናቸው። ከሶማሊያ እና ከኤርትራ ተሰደው በኢትዮጵያ የተጠለሉ ስደተኞች በሁለተኝነት እና በሶስተኝነት ተቀምጠዋል። ኢትዮጵያ በሁሉም ድንበሮቿ የጎረቤት ሀገራት ስደተኞች እንዲገቡ በሮቿን ክፍት ማድረጓን የጠቆመው የመንግስታቱ…
ተጨማሪ ያንብቡ
ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ወደ ሳዑዲ አረቢያ አቀኑ

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ወደ ሳዑዲ አረቢያ አቀኑ

ኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሳዑዲ አረቢያ የአፍሪካ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ወደሪያድ አቅንተዋል። የአገሪቱ የመረጃ ሚኒስትር የማነ ገብረ መስቀል በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው እንዳሰፈሩት ኢሳያስ ዛሬ ማለዳ ላይ ወደ ሳዑዲ አምርተዋል። አብረዋቸው ከተጓዙ የልዑካን ቡድናቸው አባላት መካከል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸው ኦስማን ሳለህ፥ የፓርቲያቸው የምጣኔ ኃብት ጉዳዮች ኃላፊ ሃጎስ ገብረህይወት እንዲሁም የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ነስረዲን ቤኪት ይገኙበታል። በጉባዔው ይታደማሉ ተብሎ ከሚጠበቁ ሌሎች የአፍሪካ መሪዎች መካከልም የኬንያው ዊሊያም ሩቶ እና የናይጄሪያው ቦላ ቲኑቡ ይገኙበታል። የሳዑዲ አረቢያ የአፍሪካ ጉባዔ ሪያድ ከተለያዩ የአህጉሪቷ አገራት እንዲሁም የአፍሪካ ኅብረትን ከመሳሰሉ ተቋማት ጋር ያላትን ግንኙነት የምታጠናክርበት ነው። ጉባኤው ተፋፍሞ የቀጠለው የጋዛ ቀውስ ጥላ ያጠላበታል ተብሎ…
ተጨማሪ ያንብቡ
የምክክር ኮሚሽኑ በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች እና በስድስት ክልሎች የተሳታፊዎች ልየታ መጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

የምክክር ኮሚሽኑ በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች እና በስድስት ክልሎች የተሳታፊዎች ልየታ መጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

ባለፉት 4 ወራት አዲስ አበባና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ በ6 ክልሎች የሃገራዊ ምክክር የተሳታፊዎች ልየታ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ሃገራዊ የምክክር ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ ኮሚሽኑ የ4 ወራት አፈጻጸም ረፖርቱን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት ያካሄደ ሲሆን  የኢትዮጵያ ሃገራዊ የምክክር ኮሚሽን የ4 ወራት አፈጻጸም ሪፖርትንም አዳምጧል፡፡ ምክክሩን ውጤታማ ለማድረግ በቅድመ ዝግጅት ስራው ከእድሮች፣ ከሃማኖት ተቋማት፣ ከሲቪክ ማህበራት፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች እና ከመምህራን ማህበር ጋር በአጋርነት እየሰራ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በመላ ሃገሪቱ እየተካሄደ ባለው የተሳታፊዎች ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ተግባር ሁለቱን ከተማ አስተዳደሮች ጨምሮ በ6 ክልሎች  ላይ በተለይ የልየታ ስራው…
ተጨማሪ ያንብቡ
አምስተኛው ዙር የኢትዮጵያ የሥነ-ሕዝብ እና ጤና ጥናት በሚቀጥሉት 3 ዓመታት ውስጥ ይካሄዳል ተባለ ::

አምስተኛው ዙር የኢትዮጵያ የሥነ-ሕዝብ እና ጤና ጥናት በሚቀጥሉት 3 ዓመታት ውስጥ ይካሄዳል ተባለ ::

በአሸናፊ አሰበ የኢትዮጵያ የሥነ ሕዝብና ጤና ዳሰሳ ጥናት በየአምስት አመቱ የሚካሄድ ሲሆን አራተኛው ጥናት እ.አ.አ በ2016 ከወጣ በኋላ ሳይወጣ ቆይቷል። የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት በበኩሉ አምስተኛው ዙር የሥነ ሕዝብና ጤና ዳሰሳ ጥናት በኮቪድ እና ሌሎች ልዩ ልዩ ምክንያቶች መሰራት ከነበረበት ጊዜ በሁለት ዓመት መጓተቱን ገልጾ በተያዘው በጀት ዓመት መጋቢት ወር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ ለመስራት አቅዶ እየተንቀሳቀስ እንደሆነ የአገልግሎቱ የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ እና የመረጃ ስርጭት ዳይሬክተር አቶ ሳፊ ገመዲ ለአዲስ ጊዜ ገልጸዋል። ከ2016 እስከ 2018 ዓ.ም በሚቆየው የስታቲስቲክስ ልማት ፕሮግራም ትግበራ ወቅት በሚካሄዱት ቆጠራዎችና ጥናቶችን በሚመለከት ሲከናወኑ በነበሩ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን የኢትዮጵያ…
ተጨማሪ ያንብቡ
የምግብ ድጋፍ አቅርቦት እገዳ ባለመነሳቱ በምግብ እጥረትና ሰብአዊ ቀውስ ላይ ያሳደረው ጫና እንደቀጠለ ነው።

የምግብ ድጋፍ አቅርቦት እገዳ ባለመነሳቱ በምግብ እጥረትና ሰብአዊ ቀውስ ላይ ያሳደረው ጫና እንደቀጠለ ነው።

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን(ኢሰመኮ) ለተፈናቃዮች እየቀረበ ያለውን የምግብ ድጋፍ አስመልክቶ  መግለጫ አውጥቷል፡፡  የአሜሪካ የዓለም አቀፍ ልማት ድርጅት (USAID) እና የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ከጥቅምት ወር 2016 ዓ.ም. ጀምሮ የምግብ ድጋፍ ለስደተኞች እንዲጀመር ማድረጋቸው በጎ እርምጃ ሆኖ፤ በአንጻሩ ለተፈናቃዮች እና ለሌሎች ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች የሚሰጠው የምግብ ድጋፍ አቅርቦት እገዳ  አለመነሳቱ በምግብ እጥረትና ሰብአዊ ቀውስ ላይ ያሳደረው ጫና እንደቀጠለ ነው ብሏል::የፌዴራል አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በበኩሉ የተሟላ እና በቂ ሰብአዊ ድጋፍ ለማድረግ ከፍተኛ የገንዘብ እጥረት ቢኖርም፣ ባለፉት ወራት በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ላሉ ተፈናቃዮች ትኩረት በመስጠት በሁለት ዙር በአፋር ክልል 96%፣ በጋምቤላ 96%፣ በትግራይ 87%፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ 73%፣…
ተጨማሪ ያንብቡ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዘመናዊ ቆጣሪዎችን እየቀየረ ነው።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዘመናዊ ቆጣሪዎችን እየቀየረ ነው።

በአሸናፊ አሰበ ደምበኞች በቀላሉ አፕልኬሽኑን ሞባይላቸዉ ላይ በመጫን ያላቸዉን ወርሃዊ የፍጆታ ሂሳብ በቀላሉ ለማወቅ፣ ከቆጣሪ ንባብ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ቅሬታዎችን  ለማስቀረት፣ የሃይል ስርቆትን ለመከላከል፣ የንባብ ስህተት ችግርን ለመቅረፍ እና ለመከላከል እንደሚያስችል የተነገረለት የዘመናዊ ቆጣሪ ቅየራ ስራ ሁለተኛ ዙር እንደተጀመረ  የፕሮጀክቱ ሃላፊ አቶ ጩመላ ሣሙኤል ለአዲስ ጊዜ ተናግረዋል። የመጀመሪያው ትግበራ ሚያዚያ 2015 ዓም መጀመሩን እና በሙከራው ሂደት 5000 የስማርት ቆጣሪዎችን ማዳረስ መቻሉን የተናገሩት አቶ ሣሙኤል የፕሮጀክቱ ትግበራ በዋናነት የተጀመረው ከፍተኛ ሃይል ተጠቃሚ በሆኑ ወይም የሃይል ፍጆታቸው ከ 25 ኪሎ ዋት(KW) በላይ በሚጠቀሙ የማሕበረሰብ ክፍሎች ላይ ሲሆን በሁለተኛው ዙር ትግበራ 45 ሺህ ነባር ቆጣሪዎችን በ6 ወር ጊዜ ውስጥ…
ተጨማሪ ያንብቡ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ስምንት አባላት ያሉት የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ዕጩ መልማይ ኮሚቴ ሰየሙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ስምንት አባላት ያሉት የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ዕጩ መልማይ ኮሚቴ ሰየሙ

ሰኞ ጥቅምት 26 / 2016 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ስምንት አባላት ያሉት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ዕጩ መልማይ ኮሚቴ ሰይመዋል። የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 102 እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ 1133/2011 አንቀፅ 5/1 ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዕጩ የስራ አመራር ቦርድ አባላት የሚመለምል ገለልተኛ ኮሚቴ እንደሚሰይሙ ይደነግጋል። በዚሁ መሰረት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የተሰየሙ የዕጩ ሰብሳቢ መልማይ ኮሚቴ አባላት፡- 1.  ቀሲስ ታጋይ ታደለ…………….. ሰብሳቢ 2.  ተከተል ዮሐንስ (ፕ/ር) ………….አባል 3.  ባዩህ በዛብህ…………. አባል 4.  ዮሐንስ በንቲ (ዶ/ር) …………. አባል 5.  ካሳሁን ፎሎ…………. አባል 6.  ርግበ ገብረሃዋርያ…………. አባል 7.  እንግዳዬ እሸቴ…………. አባል 8.  መላኩ እዘዘው (ኢ/ር) ………….…
ተጨማሪ ያንብቡ