ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ መንግሥት እና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ሌላ ዙር ውይይት ይጀምራሉ የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገለፁ::
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ) ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ያለ ስምምነት የተጠናቀቀውን የኢትዮጵያ መንግሥት እና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት የሰላም ድርድርን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ አውጥተዋል። ዶ/ር ወርቅነህ በቀጠናው ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ውይይት እና ድርድር ያለውን ወሳኝ ሚና እንደሚገነዘቡ ገልጸዋል። ኢጋድ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የሰላም ውይይት ላይ በቅርበት ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ዋና ስራ አስፈፃሚው፣ በማንኛውም የድርድር ሂደት ውስጥ የማይቀር የፈተና ጊዜያት እንዳሉ እንደሚገነዘቡ መሰል የሽምግልና ሂደቶችን ልምድ በመንተራስ ገልጸዋል። ዶ/ር ወርቅነህ ሁለቱም ተደራዳሪ ቡድኖች አለመግባባቶችን ለመፍታት ሰላማዊ ውይይት ማድረጋቸውን አመስግነው ለኢጋድ የቴክኒክ ቡድን እና ታዛቢዎች በተለይ ደግሞ የአሜሪካ እና የኖርዌይ…
