“ሜታ በትግራይ ተወላጆች ላይ ለሚደርሰው ከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰት አስተዋጽኦ አድርጓል” አምነስቲ ኢንተርናሽናል
በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅት የትግራይ ተወላጆች ላይ በማነጣጠር ለተሰነዘሩ ማንነት ተኮር ጥቃቶች የፌስቡክ እናት ኩባንያ የሆነው ሜታ ተባባሪ ሆኗል ሲል የአለም ዓቀፉ የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ወቀሰ፡፡ አምነስቲ ትናንት ጥቅምት 20/2016 ይፋ ባደረገው ሪፖርቱ "ሜታ በሰሜን ኢትዮጵያ ለሚፈጸሙ የሰብአዊ መብት ረገጣዎች ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል" ያለ ሲሆን፤ ኩባንያው ጥላቻ እና ጥቃትን የሚያበረታቱ ይዘቶችን በበቂ ሁኔታ መቆጣጠርና መግታት አለመቻሉን ገልጿል፡፡ በዚህም “ፌስቡክ የሚከተለው ደካማ የንግድ ሞዴል እና መረጃዎችን የመቆጣጠር እንቅስቃሴ፤ በትግራይ ተወላጆች ላይ ያነጣጠሩ የጥላቻ እና የቅስቀሳ ዘመቻዎችን እንዳይቆጣጠር አድርጎታል” ያለ ሲሆን፤ ከዚህም ጋር ተያይዞ በሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት ወቅት በትግራይ ማህበረሰብ ላይ ለደረሰው ግፍ ኩባንያው የራሱን…
