አዲስ ዜና

መንግስት ከፋኖ መሪዎች ጋር እንዲነጋገር ጥሪ ቀረበ።

መንግስት ከፋኖ መሪዎች ጋር እንዲነጋገር ጥሪ ቀረበ።

10/04/2016 ለዓለም አሰፋ መንግስት ከፋኖ መሪዎች ጋር ይነጋገር ሲል ክራይሲስ ግሩፕ ጥሪ አቀረበ። በምዕራብ ሀገራት ባሉ ፖሊሲ አውጭዎች ተደማጭነት  ያለው የሀሳብ አመንጭ ተቋም ክራይሲስ ግሩፕ የአማራ ክልል ግጭት በአፋጣኝ መፍትሔ የማያገኝ ከሆነ ለሀገሪቷ አደገኛ ይሆናል ብሏል። ተቋሙ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ነፍጥ ካነገቡ የክልሉ ታጣቂዎች ጋር እንዲደራደሩ ምክር ለግሷል። መቀመጫውን በቤልጂየሟ መዲና ብራስልስ ያደረገዉ መንግስታዊ ያልሆነዉ ይህ ተቋም በዓለም ዙርያ ያሉ ቀውሶችን በመመርመር ትንታኔዎችን ያቀርባል፤ በመንግስታት ፖሊሲ አርቃቂዎች፥ በምሁራን እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ትንታኔዎቹ ተደማጭነት አላቸው። ድርጅቱ የአማራ ክልል ግጭትን አስመልክቶ ባወጣዉ  መግለጫ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በሦስቱ ክልሎች በኦሮሚያ፥ በትግራይ እና አሁን ደግሞ በአማራ መንግስትን የሚቃወሙ…
ተጨማሪ ያንብቡ

በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና የበረሃ አንበጣና ድንበር ተሻጋሪ ተባዮች ስጋት ናቸው ተብሏል።

03/2016 በተለይ ባለፉት አራት አመታት በቀጠናው ክፉኛ የአንበጣ መንጋ ተከስቶ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የማዕከሉ ሪፓርት አመላክቷል። በጎረቤት ኬንያ ምዕራባዊ ክፍል በተገባደደው የፈረንጆቹ 2023 ብቻ 5.5 ትሪሊዮን ዶላር የሚገመት እህል በወፎች ወድሟል። ይህም በቶን ሲሰላ 60ቶን ገደማ ነው ተብሏል። ይህ ይፋ የተደረገው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የአየር ንብረት ትንበያ እና ትግበራ ማዕከል ICPAC ከኢጋድ አባለ ሀገራት ለተወጣጡ ጋዜጠኞች በሰጠው ስልጠና ላይ ነው። ስልጠናው በዋናነት የበረሃ አንበጣና በሌሎች ድንበር ተሻጋሪ ፀረ ሰብል ተባዮች ላይ ያተኮረ ነው። በወፎች ከሚጠቁ የሰብል አይነቶች ውስጥ ማሽላ፣ስንዴ፣ሩዝ ጤፍ እና ገብስ በግባር ቀደምትነት ይጠቀሳሉ።የሙቀት መጠን በከፍተኛ ደረጃ መጨመር ለተባዮች መፈልፈል እና…
ተጨማሪ ያንብቡ
በትላንትናው ዕለት ከሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትስር ዴኤታነታቸው የተነሱትአቶታዬደንደአ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጸጥታናደህንነት የጋራ ግብረኃይል ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።

በትላንትናው ዕለት ከሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትስር ዴኤታነታቸው የተነሱትአቶታዬደንደአ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጸጥታናደህንነት የጋራ ግብረኃይል ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።

ታህሳስ02/2016 ላለፉት ሁለት ዓመታት ገደማ የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ በመሆን ሲሰሩ የቆዩት አቶ ታዬ፤ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በተጻፈ ደብዳቤ ከኃላፊነታቸው የተነሱት ትላንት ሰኞ ታህሳስ 1፤ 2016 ነበር። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ደብዳቤ ሚኒስትር ዴኤታው ከስልጣናቸው የተነሱበትን ምክንያት ባይጠቅስም፤ ይህንኑ ተከትሎ አቶ ታዬ በይፋዊ የፌስቡክ ገጻቸው ባወጡት ጹሁፍ ግን ከስልጣናቸውን የተነሱት “የወንድማማቾች መገዳደል ይቆም ዘንድ ለሰላም በመወገናቸው” መሆኑን አስፍረው ነበር።  የጸጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ በዛሬው መግለጫው፤ አቶ ታዬ በተመደቡበት ከፍተኛ የመንግስት ስልጣን ላይ ሆነው መንግስትን “ገዳይ እና ጨፍጫፊ” እያሉ “በተደጋጋሚ ሲወቅሱ” መደመጣቸውን ጠቅሷል። ሆኖም በተግባር “ከሽብርተኞች፣ ጽንፈኞች እና ነፍሰ ገዳዮች ጋር” በተግባር “የጥፋት ትስስር የነበራቸው” ራሳቸው አቶ ታዬ መሆናቸውን…
ተጨማሪ ያንብቡ
ኢትዮጵያን የማዳን መድረክ በሚል ስያሜ የተሰባሰቡ እና በውጭ ሃገራት  በተለያየ ዘርፍ የሚያገለግሉ ምሁራን ኢትዮጵያ ከገባችበት ፖለቲካዊና ሀገራዊ ቀውስ ሊታደጋት ይችላል  ያሉትን መፍትሄ የያዘ ፍኖተ ካርታ አዘጋጅተው  የተለያዩ አካላትን ለውይይት ጋብዘዋል፡፡

ኢትዮጵያን የማዳን መድረክ በሚል ስያሜ የተሰባሰቡ እና በውጭ ሃገራት  በተለያየ ዘርፍ የሚያገለግሉ ምሁራን ኢትዮጵያ ከገባችበት ፖለቲካዊና ሀገራዊ ቀውስ ሊታደጋት ይችላል  ያሉትን መፍትሄ የያዘ ፍኖተ ካርታ አዘጋጅተው  የተለያዩ አካላትን ለውይይት ጋብዘዋል፡፡

በተለያዩ ክፍላተ ሃገራት የሚኖሩት እኒህ ምሁራን የኢትዮጵያን አሁናዊ ሁኔታ እና ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚ ከእጇ ያመለጡ የዲሞክራሲ የሽግግር አማራጮችን በማሳየት አሁንም መንግስትን ጨምሮ  በሰላማዊም ሆነ በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ሃይሎች ተቀራርበው ካልተነጋገሩ እና ካልተወያዩ ተመሳሳይ የታሪክ ኪሳራ ላይ እንወድቃለን ብለዋል፡፡ ተጨባጭ ሁኔታዎችን በማጤን እና በመመርመር ስድስት የይሆናል አማራጮችን ያቀረበው ሰነዱ ለመንግሰት አስፈፃሚዎችም እንደደረሰ የጥናት ቡድኑ አስተባባሪዎች ትናንት በሃገር ውስጥ ለሚገኙ ጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ ሰምተናል፡፡ በዚህ ሰነድ ዙሪያ የመንግስት አስፈጻሚያንንን ጨምሮ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ምሁራን፣ የመገናኛብዙኃን ባለሞያዎች እና ስለሃገር ግድ የሚላቸው ሁሉ እንዲወያዩ እና እንዲመካካሩ ያቀረብነውን አማራጭ የመፍትሄ ሃሳብም እንዲመለከቱት እንጋብዛለን ብለዋል፡፡ save-Ethiopia-Road-Map-2Download
ተጨማሪ ያንብቡ
“ተቆርቋሪ ያጣው የንጹሃን ደም በአርያም ይጮሃል” እናት ፓርቲ

“ተቆርቋሪ ያጣው የንጹሃን ደም በአርያም ይጮሃል” እናት ፓርቲ

ህዳር 20/2016 ዓ.ም “ተቆርቋሪ ያጣው የንጹሃን ደም በአርያም ይጮሃል” ሲል በሰጠው ርዕስ እናት ፓርቲ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይ ንጹሐን ዜጎች ላይ የደረሰውን ጥቃት አስመልክቶ በዛሬው ዕለት መግለጫ አውጥቷል። ፓርቲው በምሥራቅ አርሲ ሽርካ ወረዳ በሶሌ መድኃኔዓለም እና ሴሮ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ኅዳር 13 ቀን 2016 በተፈጸመ ጅምላ ጭፍጨፋ 27 የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይ ንጹሐን ዜጎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን ከአካባቢው ነዋሪዎች መረዳቱን ገልጿል። “ይኼው ጥቃት ቀጥሎ ኅዳር 17 ቀን 2016 ደግሞ ስምንት ሰዎች በተመሳሳይ መልኩ ሲገደሉ በድምሩ 35 የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይ ንጹሐን ዜጎች መገደላቸውን አረጋግጫለው” በማለት ፓርቲው አክሏል። በርካቶችም ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው የገለጸው ፓርቲው በዚህ ጥቃት ነፍሰጡር ሴትን…
ተጨማሪ ያንብቡ
ህዳር 30 በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ተጠራ

ህዳር 30 በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ተጠራ

ህዳር 19/2016 "ጦርነት ይቁም፣ ሰላም ይስፈን፣ መከላከያ ሰራዊቱ በአስቸኳይ ወደካምፕ ይግባ" በሚል መሪ ቃል ለህዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ መጠራቱን አዲስ ጊዜ ማረጋገጥ ችላለች፡፡ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት የሰላማዊ ሰልፍ እና የአደባባይ ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል የገባው የሰልፍ ጥሪ ደብዳቤ እንደሚያብራራው፣ ሰልፉ ከተዘጋጀበት ዋንኛ ዓላማዎች መካከል ቀዳሚው "የመከላከያ ሰራዊቱ በኦሮሚያ እና በአማራ ክልል ውስጥ በመግባት ደም አፋሳሽ ተግባር ውስጥ በመሆኑ ከተሰጠው የሀገር ሉዓላዊነት የማስጠበቅ ሚና ውጭ ከሚያደርገው ዘመቻ በመቆጠብ ወደጠቅላይ ጦር ሰፈሩ እንዲገባ የሚጠይቅ" ነው፡፡ የሰላማዊ ሰልፉ አስተባባሪዎች በደብዳቤው ላይ እንደገለጹት የጥሪው ዓላማዎች መከላከያ ሰራዊቱን የሚመለከቱ ብቻ ሳይሆኑ፣ "በአዲስ አበባ፣ በኦሮሚያ…
ተጨማሪ ያንብቡ
በሀዲያ ዞን ባዳዋቾ ክላስተር  ትምህርት ባለመጀመሩ ተማሪዎች  ሰላማዊ  ሰልፍ አካሄዱ ።

በሀዲያ ዞን ባዳዋቾ ክላስተር  ትምህርት ባለመጀመሩ ተማሪዎች  ሰላማዊ  ሰልፍ አካሄዱ ።

የመምህራን ደመወዝ ከሀምሌ ወር ጀምሮ ባለመከፈሉ ምክንያት፤ በጉምቦረ ወረዳ ፣በምዕራብ ሶሮ ወረዳ ፣ በግቤ ወረዳ፣ በምስራቅ በደዋቾ ፣ምዕራብ በደዋቾ፣ በሆማቾ ና ሾኔ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም በአማካ ወረዳ የትምህርት ስራ ሙሉ በሙሉ ቆሞ ይገኛል። ነገር ግን እስካሁን ድረስ ምንም አይነት መፍትሔ ከመንግስት ባለመሰጠቱ ምክንያት ተማሪዎች  ቅሬታቸውን በሰላማዊ ሰልፍ ገልፀዋል። የተማሪዎች ወላጆችና መምህራን ይህ በሀድያ ዞን ሁለት  አይነት መንግስት መኖሩን ያመለክታል ያሉ ሲሆን  ሆን ተብሎ  ከለይ በተጠቀሱ ወረዳዎች ፤ ከተማ  አስተዳደሩ  የትዉልድ  ክፍተት እንዲፈጠር ያደረገ ሴራ ሲሉ መንግስትን ተችተዋል።  ትምህርት  በሌሞ በሆሳዕና ከተማ  እና በፎንቆ አልቆመም፤  የመምህራን ደመወዝ እዛ እየተከፈለ  እኛ ጋር የለም የሚሉት መምህራን ፤ይህም ከበጀት እጥረት…
ተጨማሪ ያንብቡ
“ያደጉት ሃገራት የገቡትን ቃል እንደሚከውኑት ከአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤው ይጠበቃል” አቶ ነመራ ገበየሁ

“ያደጉት ሃገራት የገቡትን ቃል እንደሚከውኑት ከአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤው ይጠበቃል” አቶ ነመራ ገበየሁ

ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ130 በላይ ሀገራት የሚሳተፉበት 28ተኛው የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ከህዳር 20 - ታህሳስ 2 በዱባይ እንደሚካሄድ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ አቶ ነመራ ገበየሁ ገለጹ። ጉባኤው በዓመት አንድ ጊዜ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስተባባሪነት የሚዘጋጅ ሲሆን ኢትዮጵያን በሚወክለው ልኡክም ዝግጅት እንደተደረገ ተነግሯል። በአጠቃላይ ለ12 ቀናት በሚቆየው ጉባኤ ከህዳር 20 - 21 የሃገራት መሪዎች የሚሳተፉበት ጉባኤ ሲሆን መሪዎችም የሀገራቸውን የአየር ንብረት ለውጥ ፖሊሲዎችን እንደሚያስተዋውቁ እና በመሪ ደረጃ ሊነሱ የሚገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ፓሊሲዎችን እንደሚያስተዋውቁ ይጠበቃል። በቀሪው የጉባኤው ወቅትም መሪዎች በሚያስቀምጡት መመሪያ መሰረት ውይይቶች እንደሚቀጥሉ ሚኒስትር ዴኤታው አስታውቀዋል። በጉባኤው እ.አ.አ በ2015 ተደርጎ በነበረው የፓሪሱ የአየር…
ተጨማሪ ያንብቡ
ከአብን የለቀቁ አባላት “ንስር” ፓርቲን ሊመሰርቱ እንደሆነ ገለጹ

ከአብን የለቀቁ አባላት “ንስር” ፓርቲን ሊመሰርቱ እንደሆነ ገለጹ

ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የለቀቁ አባላትን ያሰባሰበ የፖለቲካ ፓርቲ ሊመሰረት እንደሆነ የአደራጅ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አንተነህ ስለሺ ለአዲስ ጊዜ ገለጹ። ‹‹የአማራ ሕዝብ ንስር ፓርቲ›› በሚል ስም የተደራጀው ይህ አዲስ ፓርቲ ሐሙስ ህዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ራስ አምባ ሆቴል ምሥረታውን ይፋ እንደሚያደርግ ተነግሮለታል፡፡ ሐምሌ 2 ቀን 2015 ዓ.ም 245 መሥራች አባላት ተሰባስበው በወሰኑት መሠረት ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዕውቅና ጥያቄ ማቅረቡንና ነሐሴ 11 ቀን 2015 ዓ.ም. ቅድመ ዕውቅና ሰርተፊኬት እንደተሰጠው የፓርቲው አደራጅ ለአዲስ ጊዜ ጨምረው ተናግረዋል፡፡ ከክልል ባለፈ አገር አቀፍ ዕውቅና ለማግኘት እየሠሩ መሆኑንም አያይዘው ገልጸዋል፡፡ የአደራጅ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ አንተነህ ስለሺ የመመሥረቻ ጉባዔ…
ተጨማሪ ያንብቡ
ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ መንግሥት እና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ሌላ ዙር ውይይት ይጀምራሉ የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገለፁ::

ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ መንግሥት እና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ሌላ ዙር ውይይት ይጀምራሉ የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገለፁ::

የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ) ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ያለ ስምምነት የተጠናቀቀውን የኢትዮጵያ መንግሥት እና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት የሰላም ድርድርን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ አውጥተዋል። ዶ/ር ወርቅነህ በቀጠናው ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ውይይት እና ድርድር ያለውን ወሳኝ ሚና እንደሚገነዘቡ ገልጸዋል። ኢጋድ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የሰላም ውይይት ላይ በቅርበት ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ዋና ስራ አስፈፃሚው፣ በማንኛውም የድርድር ሂደት ውስጥ የማይቀር የፈተና ጊዜያት እንዳሉ እንደሚገነዘቡ መሰል የሽምግልና ሂደቶችን ልምድ በመንተራስ ገልጸዋል። ዶ/ር ወርቅነህ ሁለቱም ተደራዳሪ ቡድኖች አለመግባባቶችን ለመፍታት ሰላማዊ ውይይት ማድረጋቸውን አመስግነው ለኢጋድ የቴክኒክ ቡድን እና ታዛቢዎች በተለይ ደግሞ የአሜሪካ እና የኖርዌይ…
ተጨማሪ ያንብቡ