አዲስ ጊዜ

228 Posts
አቶ ተመስገን ጥሩነህ የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሁነው ተሾሙ። አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነዋል።

አቶ ተመስገን ጥሩነህ የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሁነው ተሾሙ። አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነዋል።

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ ስብሰባ የአቶ ተመስገን ጥሩነህን ም/ጠ/ሚኒስትርነት እና የአምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሹመት አጽድቋል። ጠ/ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የአቶ ተመስገን ጥሩነህን እና የአምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴን የሥራ ልምድ ዘርዝረው ለምክር ቤቱ ባቀረቡት መሰረት ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ሹመቶቹን አጽድቋል።
ተጨማሪ ያንብቡ
”በመቶ የሚቆጠሩ እስረኞች ብቻ ናቸው ያሉት ” ጠ/ሚኒስትር ዐብይ አህመድ

”በመቶ የሚቆጠሩ እስረኞች ብቻ ናቸው ያሉት ” ጠ/ሚኒስትር ዐብይ አህመድ

ትናንት በህዝብተወካዮች ም/ቤት  የኢትዮጵያን የፀጥታ ሁኔታበሚመለከት ማብራሪያ ያቀረቡት ጠ/ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የኢትዮጵያን ሰላም የሚያውኩት አካላት  የፖለቲካ ፍላጎት የማሳኪያ ልምምድ የሌላቸው ናቸው ሲሉ የተቹ ሲሆን ከሸኔ ጋር በታንዛንያ የተደረገው ድርድር ያለ ውጤት በመጠናቀቁ ምክንያት ምንም ለህዝብ ይፋ ማድረግ የተቻለ ነገር የለም ብለዋል፡፡ በአማራ ክልል የሚታየውን አለመረጋጋት በተመለከተ የአማራ ሕዝብ መሠረታዊ ጥያቄዎች ልማት፣ የሕገ መንግሥት ማሻሻያ እና የወሰን ጉዳዮች ናቸው ያሉ ሲሆን ከሰላም ማስከበር ጋር በተያያዘ ግን መንግሥት በቀጣይነት ሕግ የማስከበር ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል። እጃችሁን አጣጥፋችሁ ተቀመጡ የሚለውን ጉዳይ አንስማማም አንቀበልም አናደርግም። መንግሥት ነን አቅም በፈቀደ መጠን ሕግ ለማስከበር እንሰራለን  ሲሉ አክለዋል። "ሕግ ለማስከበር ስንሰራ በየአንዳንዷ ሰከንድ…
ተጨማሪ ያንብቡ
ስታንዳርድ ባንክ በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት የባንክ ፍቃድ እንደሚጠይቅ አስታውቋል።

ስታንዳርድ ባንክ በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት የባንክ ፍቃድ እንደሚጠይቅ አስታውቋል።

ዋና መቀመጫውን በደቡብ አፍሪካ ያደረገው ባንኩ  በአፍሪካ ትልቁን ያልተነካ ገበያ እየፈለገ በሚገኝበት በዚህ ጊዜ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ከሁለት ሳምንት በኃላ ከውጭ የፋይናንስ ተቋማት የኢንቨስትመንት የባንክ ፍቃድ ማመልከቻዎችን እንደሚቀበል በመግለፁ  ጥሪውን ተቀብሎ ፍቃደኝነቱን አሳይቷል፡፡ በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ባንክ ፍቃድ ለማግኘት ዝቅተኛው የተከፈለ ካፒታል ለዉጪ ባንኮች 100 ሚሊዮን ብር እና ከባንክ ላልሆኑ የፋይናንስ ተቋማት 25 ሚሊዮን ብር ሀብት ሊኖራቸው ይገባል። ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በባንክ ዘርፍ ለመሰማራት ፍላጎት ላላቸው የውጭ ባለሀብቶች የባንክ ፈቃድ ለመስጠት ማቀዷን ባሳለፍነው ግንቦት ወር ላይ ይፋ ማድረጓ ይታወሳል፡፡ በወቅቱ የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ሰለሞን ደስታ እንዳሉት በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ከሦስት እስከ አምስት ለሚደርሱ በኢትዮጵያ…
ተጨማሪ ያንብቡ
በትግራይ ክልል፣ ሰሜን ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ ሽረ ከተማ የሚገኙ ተፈናቃዮች  የተበላሸ ፣መጥፎ ጠረን ያለው እና የነቀዘ ዱቄት ከለጋሽ ደርጅቶች መታደላቸውን ገልጸዋል።

በትግራይ ክልል፣ ሰሜን ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ ሽረ ከተማ የሚገኙ ተፈናቃዮች የተበላሸ ፣መጥፎ ጠረን ያለው እና የነቀዘ ዱቄት ከለጋሽ ደርጅቶች መታደላቸውን ገልጸዋል።

22/05/16 ላለፉት 13 ወራት የረባ ሰብአዊ እርዳታ ባለማግኘታቸው በከባድ ችግር ውስጥ እንደሚገኙ የገለፁት ተፈናቃዮቹ ፤ ከረጅም ጊዚያት በኃላ ጥር 20/2016 ዓ.ም መሰጠት የተጀመረው ዱቄት ጥራት የሌለው ፣ የተበላሽ ፣ የነቀዘና መጥፎ ጥረን ያለው መሆኑ በማስረጃ አስደግፈው አቅርበዋል።  የቴሌቪዥን ጣቢያው " ለተፈናቃዮቹ የተሰጠው ዱቄት ለምግብነት ቢያውሉት ለጤናቸው ጠንቅ እንደሚሆን የምግብ ባለሙያዎች አረጋግጠውልኛል " ብሏል።   ዱቄቱ በእርዳታ ያከፋፈሉ ለጋሽ ድርጅቶች 'ተበላሸ' ስለተባለው እህል ምላሽ እንዲሰጡ የተደረገው ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም። ጉዳዩ በጥብቅ እየተከታተለው መሆኑ የገለፀው የእንዳስላሰ ሽረ መንግስታዊ አገልግሎት ፅህፈት ቤት ፤  ዱቄቱ ያከፋፈሉ ለጋሽ ድርጅቶች ያደሉት እንዲሰበስቡና ማደል እንዲያቆሙ የሚጠይቅ ደብዳቤ መፃፉን አስታውቋል። ፅህፈት ቤቱ ለለጋሽ ድርጅቶች በፃፈው…
ተጨማሪ ያንብቡ
ባለፈው አንድ ዓመት በኢትዮጵያ ሙስና መባባሱን ዓለም አቀፍ ሪፖርት አመለከተ

ባለፈው አንድ ዓመት በኢትዮጵያ ሙስና መባባሱን ዓለም አቀፍ ሪፖርት አመለከተ

22/05/2016 በተጠናቀቀው የፈረንጆች 2023 ዓመት በኢትዮጵያ የሙስና ወንጀሎች መጨመራቸውን ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል አስታውቋል። የ180 አገራት የሙስና ነክ ወንጀሎችን በየዓመቱ የሚመዝነው ተቋም ይፋ ባደረገው የ2023 ሙሉ ዓመት ሪፖርት ኢትዮጵያ በመመዘኛዎቹ 37 ከ100 ነጥብ በማግኘት 98ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡ በተቋሙ መለከያ መሰረት ዓለም አቀፍ አማካኝ የሙስና ውጤት 43 ነጥብ ሲሆን፤ ኢትዮጵያ ከአማካኝ በታች በስድስት ነጥብ ዝቅ ብላ ትገኛለች። በትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ነጥብ አሰጣጥ መሰረት 100 ማለት ከሙስና ነጻ ማለት ሲሆን ወደ ዜሮ እየቀነሰ ሲሄድ የሙስና ወንጀሎች መጨመራቸውን አመላካች ነው። ተቋሙ የሚፈትሻቸው የሙስና ዓይነቶች ጉቦ፣ በጀቶችን ማዞር፣ የመንግሥት ስልጣንን ያለከልካይ ለግል ጥቅም ማዋል፣ የመንግስት አካላት በመንግስት ዘርፍ ሙስናን የመቆጣጠር ችሎታ፣ በመንግስት…
ተጨማሪ ያንብቡ
ፍላጎታቸውን “በነፍጥ ማስፈጸም” በሚፈልጉ ኃይሎች ላይ፤ ህግ የማስከበር እርምጃ “ተጠናክሮ” እንደሚቀጥል ብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ

ፍላጎታቸውን “በነፍጥ ማስፈጸም” በሚፈልጉ ኃይሎች ላይ፤ ህግ የማስከበር እርምጃ “ተጠናክሮ” እንደሚቀጥል ብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ

17/05/17 ገዢው ብልጽግና ፓርቲ “በነፍጥ ፍላጎታቸውን የማስፈጸም ዓላማ አላቸው” ያላቸው አካላት ላይ፣ “ህግን የማስከበር ስራ” “በተጠናከረ መንገድ እንዲካሄድ” ውሳኔ ማስተላለፉን አስታወቀ። በሀገሪቱ የተሟላ ሰላም ለማስፈን፤ ከታጣቂ ቡድኖች ጋር የተጀመሩ “ሰላማዊ አማራጮች” ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መወሰኑንም ገልጿል። ብልጽግና ፓርቲ ይህን ያስታወቀው ካለፈው ሰኞ ጥር 13፤ 2016 ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት በአዲስ አበባ ያካሄዳቸውን የስራ አስፈጻሚ እና የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባዎችን ሲያጠናቀቅ ባወጣው መግለጫ ነው። በሁለቱ ሰብሰባዎች ላይ “አበይት ሀገራዊ ጉዳዮች እና ልዩ ልዩ የፓርቲ አጀንዳዎች” ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። ፓርቲው በስብሰባዎቹ ካሳለፋቸው ውሳኔዎች መካከል በኢትዮጵያ ያለውን የሰላም እና የጸጥታ ሁኔታ የሚመለከተው ይገኝበታል። “በጠባብ ቡድናዊ ፍላጎት” የተፈጠሩ “ትስስሮች” አስከትለዋቸዋል የተባሉ ግጭቶች፤…
ተጨማሪ ያንብቡ
“በማንኛውም ጊዜ የፀጥታ ችግር ቢከሰት ሃላፊነቱን አልወስድም ” ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ

“በማንኛውም ጊዜ የፀጥታ ችግር ቢከሰት ሃላፊነቱን አልወስድም ” ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ

15/05/16 በተለያዩ ጊዜያት በፋኖ እና በመንግሥት ታጣቂዎች መካከል ውግያ የተካሄደባት የደብረ ብርሃን ከተማ በአሁኑ ወቅት አንፃራዊ ሰላም በአከባቢዉ ቢስተዋልም ባለው ነባራዊ ሁኔታ አስጊ የሆነ የፀጥታ ችግሮች አሁንም በስጋትነት ያሉ በመሆኑ በማንኛውም ወቅት የፀጥታ ችግር ቢከሰት ሃላፊነቱን እንደማይወስድ የደብረ ብርሃን ዩንቨርስቲ አስታወቀ ፡፡ ነባር ተማሪዎች እና አዳዲስ ተማሪዎች ከጥር 23ቀን 2016ዓ.ም ጀምሮ እንዲገቡ ጥሪ ያደረገው ዩኒቨርስቲው ምንም ዓይነት የፀጥታ ችግር ቢፈጠር ሃላፊነቱን እንደማይወስድ አሳውቋል። የ2016ዓ.ም የመማር የማስተማር ሂደት በአማራ ክልል ባለው የፀጥታ ስጋት ምክንያት የተስተጓጎለ መሆኑን የሚገልጹት የዩኒቨርሲቲው የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ አህመድ ሞሃመድ መስከረም ወር መጨረሻ 2016ዓ.ም የጤና ተማሪዎችን እና የ2016ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎችን እንዲሁም ጥቅምት መጨረሻ…
ተጨማሪ ያንብቡ
በኦሮሚያ ክልል “በመርዛማ ጋዝ” በብልጽግና ፓርቲ ሠራዊት ጥቃት እየተፈጸመ ነው- ኦነግ

በኦሮሚያ ክልል “በመርዛማ ጋዝ” በብልጽግና ፓርቲ ሠራዊት ጥቃት እየተፈጸመ ነው- ኦነግ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ኦነግ ትላንት ምሽት ባወጣው መግለጫ  “የብልጽግና ፓርቲ ወታደራዊ ሃይል” ሲል የጠራው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በኦሮሚያ ክልል ድሮን በመጠቀም በንጹሃን ዜጎች ላይ  ወንጀል   እየፈጸመ ነው አለ። የኦሮሞ ነጻነት ግንባር  ኦነግ  ባለፈው እሁድ ጥር 12 ቀን 2016 በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ቀርሳ ማሊማ ወረዳ ጊቢሶ ቀበሌ “የድሮን አውሮፕላኖች የመርዝ ጋዝን በመጠቀም” በሠላማዊ ሰዎች ሰፈሮች ላይ የመንግስት ኃይሎች ባደረሱት ጥቃት የበርካታ ሰዎች ህይወት ሲያልፍ የሠላማዊ ዜጎች ንብረት ወድሟል። ይህን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎችም ጥር 12 እና 13 ቀን 2016 ማለትም እሁድና ሰኞ በተፈጸሙ ጥቃቶች ፓርቲው በስም የጠቀሳቸው አምስት ሰዎችን ጨምሮ “በርካታ ንጹሐን ዜጎች” ሲሞቱ ቁጥራቸው ያልተጠቀሰ…
ተጨማሪ ያንብቡ
አስፋውን ተሰናበትነው  

አስፋውን ተሰናበትነው  

በበርካቶች ዘንድ በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ "ሞቅ ደመቅ ሸብረቅ" በምትል ንግግሩ ይታወቃል፡፡ አስፋው መሸሻ፡፡ መሸሻ ይሙት የሚለው መሃላውም አይረሳም፡፡ ከአባቱ ከአቶ መሸሻ አስፋው እና ከእናቱ ከ ወ/ሮ ዘነበወርቅ አሻግሬ ሀምሌ 1959 ዓም በአዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ ‹‹ሰሜን ማዘጋጃ  ችሎት ሰፈር››  በሚባለው አካባቢ የተወለደው አስፋው ለቤተሰቡ አምስተኛ ልጅ እንደሆነ ይነገራል።አባቱ ዲፕሎማት በመሆናቸው እና ለሥራ ጉዳይ ወደ ተለያዩ ክፍለ ዓለማት ይዘዋወሩ ስለነበር ትምህርቱን በኢትዮጵያ፣ታንዛንያ እና ኬንያ ተከታትሏል። አስፋው ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ  ከጓደኛው ዳንኤል ግዛው ጋር በኤፍ ኤም 97.1 ላይ በጋራ  "አይሬ"የተሰኘ ፕሮግራም ማዘጋጀት እና ማቅረብ ጀመረ፡፡ በአይሬ ፕሮግራሙ ተወዳጅነትን ያተረፈው አስፋው ከሃገር እስከወጣበት ጊዜ ድረስ በኤፍ ኤም 97.1…
ተጨማሪ ያንብቡ
 1 ነጥብ 7 ትሪሊየን ብር በቴሌብር ብቻ ማንቀሳቀስ ተችሏል -ኢትዮ ቴሌኮም

 1 ነጥብ 7 ትሪሊየን ብር በቴሌብር ብቻ ማንቀሳቀስ ተችሏል -ኢትዮ ቴሌኮም

14/06/2016 የቴሌ ብር አገልግሎት ከተጀመረ በኋላ በአጠቃላይ የግብይት መጠን 1 ነጥብ 7 ትሪልየን ብር በኢኮኖሚው ላይ ማንቀሳቀሱን ኢትዮ ቴሌኮም አስታወቀ። ኢትዮ ቴሌኮም ይኼን የገለጸው የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ መንፈቅ ስራ አፈጻጸሙን በዛሬው ዕለት ጥር 14 2016 በስካይ ላይት ሆቴል ባሳወቀበት መድረክ ነው። በመድረኩ ላይ የተገኙት የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ቴሌ ብር አገልግሎት ከ41 ሚሊየን በላይ ደንበኞች ማፍራቱንም ተናግረዋል፡፡እንዲሁም በቴሌብር ሳንዱቅ፣ ቴሌ ብር እንደኪሴ፣ ቴሌብር መላ እና ሌሎችም የፉይናንስ አገልግሎት 3 ነጥብ 8 ሚሊየን ደንበኞችን አፍርቶ፤ 8 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የብድር አገልግሎት እንዲሁም በቁጠባ አገልግሎት 8 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር መቀመጡ ታውቋል። በተጨማሪም ከዲጂታል…
ተጨማሪ ያንብቡ