አዲስ ዜና

ስታንዳርድ ባንክ በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት የባንክ ፍቃድ እንደሚጠይቅ አስታውቋል።

ስታንዳርድ ባንክ በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት የባንክ ፍቃድ እንደሚጠይቅ አስታውቋል።

ዋና መቀመጫውን በደቡብ አፍሪካ ያደረገው ባንኩ  በአፍሪካ ትልቁን ያልተነካ ገበያ እየፈለገ በሚገኝበት በዚህ ጊዜ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ከሁለት ሳምንት በኃላ ከውጭ የፋይናንስ ተቋማት የኢንቨስትመንት የባንክ ፍቃድ ማመልከቻዎችን እንደሚቀበል በመግለፁ  ጥሪውን ተቀብሎ ፍቃደኝነቱን አሳይቷል፡፡ በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ባንክ ፍቃድ ለማግኘት ዝቅተኛው የተከፈለ ካፒታል ለዉጪ ባንኮች 100 ሚሊዮን ብር እና ከባንክ ላልሆኑ የፋይናንስ ተቋማት 25 ሚሊዮን ብር ሀብት ሊኖራቸው ይገባል። ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በባንክ ዘርፍ ለመሰማራት ፍላጎት ላላቸው የውጭ ባለሀብቶች የባንክ ፈቃድ ለመስጠት ማቀዷን ባሳለፍነው ግንቦት ወር ላይ ይፋ ማድረጓ ይታወሳል፡፡ በወቅቱ የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ሰለሞን ደስታ እንዳሉት በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ከሦስት እስከ አምስት ለሚደርሱ በኢትዮጵያ…
ተጨማሪ ያንብቡ
በትግራይ ክልል፣ ሰሜን ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ ሽረ ከተማ የሚገኙ ተፈናቃዮች  የተበላሸ ፣መጥፎ ጠረን ያለው እና የነቀዘ ዱቄት ከለጋሽ ደርጅቶች መታደላቸውን ገልጸዋል።

በትግራይ ክልል፣ ሰሜን ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ ሽረ ከተማ የሚገኙ ተፈናቃዮች የተበላሸ ፣መጥፎ ጠረን ያለው እና የነቀዘ ዱቄት ከለጋሽ ደርጅቶች መታደላቸውን ገልጸዋል።

22/05/16 ላለፉት 13 ወራት የረባ ሰብአዊ እርዳታ ባለማግኘታቸው በከባድ ችግር ውስጥ እንደሚገኙ የገለፁት ተፈናቃዮቹ ፤ ከረጅም ጊዚያት በኃላ ጥር 20/2016 ዓ.ም መሰጠት የተጀመረው ዱቄት ጥራት የሌለው ፣ የተበላሽ ፣ የነቀዘና መጥፎ ጥረን ያለው መሆኑ በማስረጃ አስደግፈው አቅርበዋል።  የቴሌቪዥን ጣቢያው " ለተፈናቃዮቹ የተሰጠው ዱቄት ለምግብነት ቢያውሉት ለጤናቸው ጠንቅ እንደሚሆን የምግብ ባለሙያዎች አረጋግጠውልኛል " ብሏል።   ዱቄቱ በእርዳታ ያከፋፈሉ ለጋሽ ድርጅቶች 'ተበላሸ' ስለተባለው እህል ምላሽ እንዲሰጡ የተደረገው ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም። ጉዳዩ በጥብቅ እየተከታተለው መሆኑ የገለፀው የእንዳስላሰ ሽረ መንግስታዊ አገልግሎት ፅህፈት ቤት ፤  ዱቄቱ ያከፋፈሉ ለጋሽ ድርጅቶች ያደሉት እንዲሰበስቡና ማደል እንዲያቆሙ የሚጠይቅ ደብዳቤ መፃፉን አስታውቋል። ፅህፈት ቤቱ ለለጋሽ ድርጅቶች በፃፈው…
ተጨማሪ ያንብቡ
ባለፈው አንድ ዓመት በኢትዮጵያ ሙስና መባባሱን ዓለም አቀፍ ሪፖርት አመለከተ

ባለፈው አንድ ዓመት በኢትዮጵያ ሙስና መባባሱን ዓለም አቀፍ ሪፖርት አመለከተ

22/05/2016 በተጠናቀቀው የፈረንጆች 2023 ዓመት በኢትዮጵያ የሙስና ወንጀሎች መጨመራቸውን ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል አስታውቋል። የ180 አገራት የሙስና ነክ ወንጀሎችን በየዓመቱ የሚመዝነው ተቋም ይፋ ባደረገው የ2023 ሙሉ ዓመት ሪፖርት ኢትዮጵያ በመመዘኛዎቹ 37 ከ100 ነጥብ በማግኘት 98ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡ በተቋሙ መለከያ መሰረት ዓለም አቀፍ አማካኝ የሙስና ውጤት 43 ነጥብ ሲሆን፤ ኢትዮጵያ ከአማካኝ በታች በስድስት ነጥብ ዝቅ ብላ ትገኛለች። በትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ነጥብ አሰጣጥ መሰረት 100 ማለት ከሙስና ነጻ ማለት ሲሆን ወደ ዜሮ እየቀነሰ ሲሄድ የሙስና ወንጀሎች መጨመራቸውን አመላካች ነው። ተቋሙ የሚፈትሻቸው የሙስና ዓይነቶች ጉቦ፣ በጀቶችን ማዞር፣ የመንግሥት ስልጣንን ያለከልካይ ለግል ጥቅም ማዋል፣ የመንግስት አካላት በመንግስት ዘርፍ ሙስናን የመቆጣጠር ችሎታ፣ በመንግስት…
ተጨማሪ ያንብቡ
ፍላጎታቸውን “በነፍጥ ማስፈጸም” በሚፈልጉ ኃይሎች ላይ፤ ህግ የማስከበር እርምጃ “ተጠናክሮ” እንደሚቀጥል ብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ

ፍላጎታቸውን “በነፍጥ ማስፈጸም” በሚፈልጉ ኃይሎች ላይ፤ ህግ የማስከበር እርምጃ “ተጠናክሮ” እንደሚቀጥል ብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ

17/05/17 ገዢው ብልጽግና ፓርቲ “በነፍጥ ፍላጎታቸውን የማስፈጸም ዓላማ አላቸው” ያላቸው አካላት ላይ፣ “ህግን የማስከበር ስራ” “በተጠናከረ መንገድ እንዲካሄድ” ውሳኔ ማስተላለፉን አስታወቀ። በሀገሪቱ የተሟላ ሰላም ለማስፈን፤ ከታጣቂ ቡድኖች ጋር የተጀመሩ “ሰላማዊ አማራጮች” ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መወሰኑንም ገልጿል። ብልጽግና ፓርቲ ይህን ያስታወቀው ካለፈው ሰኞ ጥር 13፤ 2016 ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት በአዲስ አበባ ያካሄዳቸውን የስራ አስፈጻሚ እና የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባዎችን ሲያጠናቀቅ ባወጣው መግለጫ ነው። በሁለቱ ሰብሰባዎች ላይ “አበይት ሀገራዊ ጉዳዮች እና ልዩ ልዩ የፓርቲ አጀንዳዎች” ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። ፓርቲው በስብሰባዎቹ ካሳለፋቸው ውሳኔዎች መካከል በኢትዮጵያ ያለውን የሰላም እና የጸጥታ ሁኔታ የሚመለከተው ይገኝበታል። “በጠባብ ቡድናዊ ፍላጎት” የተፈጠሩ “ትስስሮች” አስከትለዋቸዋል የተባሉ ግጭቶች፤…
ተጨማሪ ያንብቡ
“በማንኛውም ጊዜ የፀጥታ ችግር ቢከሰት ሃላፊነቱን አልወስድም ” ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ

“በማንኛውም ጊዜ የፀጥታ ችግር ቢከሰት ሃላፊነቱን አልወስድም ” ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ

15/05/16 በተለያዩ ጊዜያት በፋኖ እና በመንግሥት ታጣቂዎች መካከል ውግያ የተካሄደባት የደብረ ብርሃን ከተማ በአሁኑ ወቅት አንፃራዊ ሰላም በአከባቢዉ ቢስተዋልም ባለው ነባራዊ ሁኔታ አስጊ የሆነ የፀጥታ ችግሮች አሁንም በስጋትነት ያሉ በመሆኑ በማንኛውም ወቅት የፀጥታ ችግር ቢከሰት ሃላፊነቱን እንደማይወስድ የደብረ ብርሃን ዩንቨርስቲ አስታወቀ ፡፡ ነባር ተማሪዎች እና አዳዲስ ተማሪዎች ከጥር 23ቀን 2016ዓ.ም ጀምሮ እንዲገቡ ጥሪ ያደረገው ዩኒቨርስቲው ምንም ዓይነት የፀጥታ ችግር ቢፈጠር ሃላፊነቱን እንደማይወስድ አሳውቋል። የ2016ዓ.ም የመማር የማስተማር ሂደት በአማራ ክልል ባለው የፀጥታ ስጋት ምክንያት የተስተጓጎለ መሆኑን የሚገልጹት የዩኒቨርሲቲው የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ አህመድ ሞሃመድ መስከረም ወር መጨረሻ 2016ዓ.ም የጤና ተማሪዎችን እና የ2016ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎችን እንዲሁም ጥቅምት መጨረሻ…
ተጨማሪ ያንብቡ
 1 ነጥብ 7 ትሪሊየን ብር በቴሌብር ብቻ ማንቀሳቀስ ተችሏል -ኢትዮ ቴሌኮም

 1 ነጥብ 7 ትሪሊየን ብር በቴሌብር ብቻ ማንቀሳቀስ ተችሏል -ኢትዮ ቴሌኮም

14/06/2016 የቴሌ ብር አገልግሎት ከተጀመረ በኋላ በአጠቃላይ የግብይት መጠን 1 ነጥብ 7 ትሪልየን ብር በኢኮኖሚው ላይ ማንቀሳቀሱን ኢትዮ ቴሌኮም አስታወቀ። ኢትዮ ቴሌኮም ይኼን የገለጸው የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ መንፈቅ ስራ አፈጻጸሙን በዛሬው ዕለት ጥር 14 2016 በስካይ ላይት ሆቴል ባሳወቀበት መድረክ ነው። በመድረኩ ላይ የተገኙት የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ቴሌ ብር አገልግሎት ከ41 ሚሊየን በላይ ደንበኞች ማፍራቱንም ተናግረዋል፡፡እንዲሁም በቴሌብር ሳንዱቅ፣ ቴሌ ብር እንደኪሴ፣ ቴሌብር መላ እና ሌሎችም የፉይናንስ አገልግሎት 3 ነጥብ 8 ሚሊየን ደንበኞችን አፍርቶ፤ 8 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የብድር አገልግሎት እንዲሁም በቁጠባ አገልግሎት 8 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር መቀመጡ ታውቋል። በተጨማሪም ከዲጂታል…
ተጨማሪ ያንብቡ
 በትግራይክልል  28% ህፃናት የምግብ እጥረት አጋጥሟቸዋል።

 በትግራይክልል  28% ህፃናት የምግብ እጥረት አጋጥሟቸዋል።

አሸናፊ አሰበ 14/06/2016 በትግራይ ክልል ከተከሰተው አስከፊ ድርቅ ጋር ተያይዞ   ህፃናት በከፍተኛ ደረጃ በምግብ እጥረት እየተጎዱ ነው የክልሉ ጤና ቢሮ ከ ትግራይ ክልል አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ጋር በመተባበር በጋራ አካሄድኩት ባላው ጥናት 26% የክልሉ ህጻናት መካከለኛ እና አጣዳፊ የምግብ እጥረት እንዳጋጠማቸው መረጋገጡን በትግራይ ክልል ጤና ቢሮ የ ስነ-አመጋገብ ጉዳይ ቡድን አስተባባሪ አቶ መንገሻ ባህረሥላሴ ለ አዲስ ጊዜ ተናግረዋል፡፡ እንደ ሃላፊው ገለጻ ጥናቱ የተካሄደው በትግራይ ክልል ውስጥ ካሉ ወረዳዎች ውስጥ በ 36 ቱ ብቻ ሲሆን በምግብ እጥረት ምክንያት በሆስፒታሎች ውስጥ ሞት እየተመዘገበ መሆኑንም አክለዋል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ ከሚያስተዳድራቸው 73 ወረዳዎች ውስጥ ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች የሚገኘው ድጋፍ…
ተጨማሪ ያንብቡ
“በኢትዮጵያ በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች ቁጥር የሚያሳየው፣ የሀገሪቱ ሁኔታ ለመገናኛ ብዙሃን አመቺ አለመሆኑን ነው”ሲፒጄ

“በኢትዮጵያ በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች ቁጥር የሚያሳየው፣ የሀገሪቱ ሁኔታ ለመገናኛ ብዙሃን አመቺ አለመሆኑን ነው”ሲፒጄ

12/06/2016 ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን በማሰር ከአፍሪካ ሃገራት ሶስተኛ ደረጃ መያዟን ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች (ሲፒጄ) ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርቱ አስታውቋል። በአፍሪካ በታሳሪ ጋዜጠኞች ቁጥር ኤርትራ ቀዳሚ ስትሆን ግብፅ ሁለተኛዋ ሃገር ሁናለች፡፡ ሲፒጄ ዓመታዊ ሪፖርቱን ባጠናቀረበት ባለፈው ህዳር ወር መጨረሻ ገደማ፤ በመላው ዓለም የታሰሩ ጋዜጠኞች ብዛት 320 እንደነበር ገልጿል።ከእነዚህም መሃል 5ቱ ሴቶች ሲሆኑ ሁለቱ ኢትዮጵያዊያን ናቸው፡፡ ይህ ቁጥር ድርጅቱ መሰል ሪፖርቶች ማዘጋጀት ከጀመረበት ከ1985 ዓ.ም. ወዲህ በከፍተኛነቱ በሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚቀመጥ መሆኑንም ጠቁሟል። በአፍሪካ እስካለፈው ህዳር መጨረሻ ድረስ ባለው የአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ፤ ቢያንስ 67 የሚሆኑ ጋዜጠኞች “ከስራቸው ጋር በተያይዘ ለእስር መዳረጋቸውን” ሲፒጄ በሪፖርቱ አመልክቷል።…
ተጨማሪ ያንብቡ
”የሶማሊያ ሉዓላዊ ግዛትን የሚመለከት ማንኛውም ስምምነት የሃገሪቱን መንግስት ይሁንታ ሊያገኝ ይገባል” ኢጋድ

”የሶማሊያ ሉዓላዊ ግዛትን የሚመለከት ማንኛውም ስምምነት የሃገሪቱን መንግስት ይሁንታ ሊያገኝ ይገባል” ኢጋድ

በእታገኘሁ መኮነን 09/05/2016 የቀጠናው ሃገራት እና የቀጠናውን ጉዳይ በትኩረት የሚከታተሉ ሁሉ በጉጉት ሲጠብቁት የነበረው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ) አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ ሐሙስ ጥር 9፤ 2016 በኡጋንዳ ኢንተቤ ከተማ ተካሂዷል፡፡ መሪዎቹ በጉባኤው ማጠናቀቂያ ላይ ባወጡት መግለጫ ''የሶማሊያ ሉዓላዊ ግዛትን የሚመለከት ማንኛውም ስምምነት የሀገሪቱን መንግስት ይሁንታ ሊያገኝ ይገባል ''  ብለዋል ፡፡መሪዎቹ ማንኛውም ግንኙነት የሶማሊያን ''ሉዓላዊነት፣ አንድነት እና የግዛት አንድነት ያከበረ ሊሆን እንደሚገባም'' አሳስበዋል። በጉባኤው ላይ የአስተናጋጇ ሀገር ኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ፣  የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሐመድ ፣የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማህማት፣ የኢጋድ ዋና ጸሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ፣ የሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ…
ተጨማሪ ያንብቡ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነ የመንገደኞች አውሮፕላን በመቐለ አሉላ አባ ነጋ አየር ማረፊያ አደጋ አጋጠመው

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነ የመንገደኞች አውሮፕላን በመቐለ አሉላ አባ ነጋ አየር ማረፊያ አደጋ አጋጠመው

09/05/2016 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነ የመንገደኞች አውሮፕላን፤ ዛሬ ሐሙስ በመቐለ አሉላ አባ ነጋ አየር ማረፊያ በሚያርፍበት ወቅት ከመንደርደሪያው መንገድ ተንሸራትቶ መውጣቱን  ሆኖም በአደጋው በመንገደኞችም ላይ ሆነ የበረራ ሰራተኞች  ላይ ምንም ጉዳት እንዳልደረሰ  አየር መንገዱ ዛሬ ከሰዓት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። በአውሮፕላኑ ላይ ጉዳት መድረሱ ተነግሯል፡፡ ጉዳት የደረሰበት የአየር መንገዱ አውሮፕላን  የበረራ ቁጥር ኢቲ 106 ሲሆን ፤ ከአዲስ አበባ የተነሳው ከቀኑ 6፡30 እደሆነ ታውቋል። ክስተቱ የደረሰው ከቀኑ ስምንት ሰዓት ከአስ8፡10  ደቂቃ ላይ እንደሆነም ተጠቁሟል። አየር መንገዱ  ለተፈጠረው ችግር ደንበኞቹን ይቅርታ ጠይቆ “የአደጋውን መንስኤ ለማወቅ ምርመራ እየተደረገ” ስለመሆኑ ተናግሯል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ