አዲስ ጊዜ

227 Posts
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ለመዲናዋ ከ465 ሺህ በላይ ሰራዊት መቋቁሙን ይፋ አደረገ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ለመዲናዋ ከ465 ሺህ በላይ ሰራዊት መቋቁሙን ይፋ አደረገ።

ረዕቡ ጥቅምት 21/2016 ይህ የተገለፀው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ከደንብ ማስከበር ባለስልጣን ጋር በጋራ በመሆን የበጀት አመቱን ሩብ አመት የስራ እቅድ አፈፃፀም ጥቅምት 21 ቀን 2016 ዓ.ም በገመገመበት ወቅት ነው፡፡ ሰራዊቱ ምንም አይነት ፋይናንስ ድጋፍ እንደማይደረግለት እና በነጻ የሚሰራ ሰራዊት መሆኑን በከተማ አስተዳደሩ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊዋ ሊዲያ ግርማ ተናግረዋል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
የ2023 የአፍሪካ የምጣኔ ኃብት ጉባዔ በመጭው ሕዳር ወር በኢትዮጵያ ይካሄዳል

የ2023 የአፍሪካ የምጣኔ ኃብት ጉባዔ በመጭው ሕዳር ወር በኢትዮጵያ ይካሄዳል

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከአፍሪካ ልማት ባንክ ጋር በመተባበር የሚያሰናዳው የ2023 የአፍሪካ የምጣኔ ሃብት ጉባዔ በኢትዮጵያ እንደሚካሄድ ተነገረ። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በመጭው ሕዳር ወር የሚከናወነው የአፍሪካ የምጣኔ ሃብት ጉባዔ በአካል እና በድረ ገጽ በቅይጥ መልኩ እንደሚሰናዳ የገለጸ ሲሆን፤ አካላዊው መድረክ ደግሞ አዲስ አበባ በሚገኘው የመንግሥታቱ ድርጅት አዳራሽ እንደሚካሄድ አስታውቋል። የአህጉሪቱ ትልቁ የምርምር እና የምጣኔ ሃብት መሰባሰቢያ የሆነው ይህ መድረክ የአህጉሪቱን ሚኒስትሮች፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተባባሪዎች እና ቁልፍ የሆኑ የመንግሥት እና የግልም ኩባንያዎች ወኪሎች እንዲሁም እውቅና ጀማሪ ተመራማሪዎችን ያሳትፉበታል ተብሏል። ጉባዔው መከናወን የጀመረው በግሪጎሪያን አቆጣጠር በ2006 ሲሆን፤ በዚህ ዓመት በዘላቂ ኢንዱስትሪያላይዜሽን ላይ ትኩረቱን እንደሚያደርግ ተነግሯል።
ተጨማሪ ያንብቡ
የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ምደባን አስመልክቶ ትምህርት ሚኒስቴር ማብራሪያ ሰጠ፡፡

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ምደባን አስመልክቶ ትምህርት ሚኒስቴር ማብራሪያ ሰጠ፡፡

 በ2015 የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ወስደው ያለፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ አሰራርን አስመልክቶ የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት የተማሪ ምደባ መስፈርቶች፡- 1. 1000 ለሚሆኑ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች፡- የምደባ ስርዓቱ በተፈጥሮም ሆነ በማህበራዊ ሳይንስ መስኮች 1000 ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን በመጀመሪያ የዩኒቨርስቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫቸው ምደባ የሚካሄድ ይሆናል። 2. ውጤት፡- የምደባ ስርዓቱ እያንዳንዱ ተማሪ ያስመዘገበውን አጠቃላይ ውጤት በምደባ ስርዓት ሂደት ውስጥ መለያ አድርጎ ይጠቀማል፡፡ የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ሌሎች ተፈጻሚ የሚሆኑ ህግና ደንቦችን ባልጣሰ መልኩ ምርጫቸውን በመጠበቅ ረገድ ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፡፡ 3. የዩኒቨርሲቲ ምርጫ፡- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የቅበላ አቅም ታሳቢ ያደረገ…
ተጨማሪ ያንብቡ
የሰላም እጦት ግብር የመሰብሰቡን ስራ አዳጋች አድርጎታል ሲል የአማራ ክልል አስታወቀ

የሰላም እጦት ግብር የመሰብሰቡን ስራ አዳጋች አድርጎታል ሲል የአማራ ክልል አስታወቀ

ጥቅምት 20/2016  የአማራ ክልላዊ መንግስት በዘንድሮ በጀት ዓመት 71 ነጥብ 61 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ ወደ ስራ የገባ ቢሆንም በክልሉ በተፈጠረው የጸጥታ ችግር ምክንያት በሩብ ዓመቱ መሰብሰብ የቻለው 6 ቢሊዮን 264 ሚሊየን ብቻ መሆኑን አስታወቀ። አብዛኛዎቹ የክልሉ ዞኖች እና ከተማ አስተዳደሮች የሚጠበቅባቸውን ገቢ በመሰብሰብ ረገድ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኙ የክልሉ የገቢዎች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ፍቅረማሪያም ማሳሰባቸውን ከክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ የማህበራዊ ትስስር ገጽ ላይ የተገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡ ገቢ ከሌለ የህክምና ተቋማት እና ት/ቤቶች ይዘጋሉ፤ የመንግስት ሠራተኞች ደመወዝ ይቆማል፤ ልማት፣ እድገት፣ ብልጽግና አይኖርም ሲሉ የክልሉ የገቢዎች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ፍቅረማሪያም ደጀኔ መናገራቸውን መረጃው አካቷል። በ2016 በጀት ዓመት 71 ነጥብ…
ተጨማሪ ያንብቡ
ጎጎትበፓርቲው አመራር አቶመላኩሳህሌላይየተፈፀመውን እገታበማውገዝ መግለጫ አወጣ፡፡

ጎጎትበፓርቲው አመራር አቶመላኩሳህሌላይየተፈፀመውን እገታበማውገዝ መግለጫ አወጣ፡፡

የጎጎት ለጉራጌ አንድነት እና ፍትህ ፓርቲ የአለም አቀፍ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ የሆኑት አቶ መላኩ ሳህሌ በቀን 14/02/2016 ዓ.ም ከቤታቸው አቅራቢያ ታፍነው መወሰዳቸው ይታወሳል ያለው ፓርቲው ጥቅምት 16 አዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ጉለሌ ምድብ ችሎት የቀረቡት አቶ መላኩ ሳህሌ ፖሊስ "ሁከትና ብጥብጥ በመፍጠር እና ከጠላት ጋር በማበር" የሚል  ክስ ቢያቀርብባቸውም ችሎቱ በ5000 ብር ዋስ እንዲወጡ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር ብሏል። በዚሁ መሰረት የዋስትና ብር ተከፍሎ አቶ መላኩ ከፖሊስ ጣቢያ ይወጣሉ ተብሎ ሲጠበቅ ፖሊስ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ወደ አዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽን አዛውሮአቸው እስካሁኑ ሰአት ድረስ በእገታ ላይ ይገኛሉ ያለው መግለጫው ፍርድ ቤት በዋስ እንዲወጡ የተፈቀደላቸውን…
ተጨማሪ ያንብቡ
የአየር ንብረት ለውጥ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተነገረ

የአየር ንብረት ለውጥ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተነገረ

በዘላቂ የልማት ግቦች እና በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የሚያጠነጥን የግማሽ ቀን አውደ-ጥናት ትናንት ጥቅምት 20 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ መካሄዱን አዲስ ጊዜ አይታለች፡፡ ኤንዳ ኢትዮጵያ በመባል በሚታወቀው እና በዋናነት በከተማ ልማት እንዲሁም በአካባቢያዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን አድርጎ በሚሰራው መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት አስተባባሪነት በተዘጋጀው በዚህ መርሀ-ግብር ላይ ጥናታዊ ጽሑፎች የቀረቡ ሲሆን በተለያዩ የዜና ማሰራጫ ተቋማት ውስጥ የሚሰሩ የመገናኛ ብዙሐን ባለሞያዎችም የውይይቱ አካል ነበሩ፡፡ የአየር ንብረት ለውጥ ምልክቶች እና እያስከተሉ ያሉት መጠነ ሰፊ ጉዳቶች በአውደ-ጥናቱ ላይ በዝርዝር ቀርበዋል፡፡ በተለይ፣ ችግሩ ከኢትዮጵያ አንጻር የተዳሰሰበት ክፍል በተሳታፊዎች ዘንድ መነጋገሪያ እንደነበር መታዘብ ተችሏል፡፡ እ.አ.አ በ2030 ዓ.ም ይሳካሉ ተብለው ግብ የተያዘላቸው…
ተጨማሪ ያንብቡ
ኢትዮጵያ የአጎዋ እድልን ዳግመኛ እንድታገኝ መንግስት ሰላም ለማምጣት መስራት አለበት ተባለ፡፡

ኢትዮጵያ የአጎዋ እድልን ዳግመኛ እንድታገኝ መንግስት ሰላም ለማምጣት መስራት አለበት ተባለ፡፡

የሰሜን ኢትዮጵያዉን ጦርነት ተከትሎ በኢትዮጵያ ላይ ከተጣሉት ማዕቀቦች ዉስጥ አንዱ የአጎዋ ነጻ የንግድ እድልን ማጣት ነው፡፡ እገዳው አሁንም አልተነሳም፡፡የኢትዮጵያ ጨርቃጨርቅ እና አልባሳት አምራቾች ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ጎሹ ነጋሽ  እንደተናገሩት ፤ የጨርቃጨርቅ እና አልባሳት ዘርፉ በእቀባዉ መጎዳቱን ተናግረዉ ኢትዮጵያ የአጎዋ እድልን ዳግመኛ እንድታገኝ ሰላም በማምጣት በኩል የቤት ስራዋን መስራት አለባት ብለዋል።እግዱ ከተላለፈ በኋላ የታጣዉን የንግድ እድል ለማካካስ የተለያዩ ስራዎች በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መሰራታቸዉን ያነሱት አቶ ጎሹ ፤ የገበያ ትስስርን መፍጠር ዋነኛዉ መሆኑን ጠቁመዋል።ሀላፊው ይህን ያሉት በኢትዮጵያ ባሉ የጨርቃጨርቅ አምራቾች የንግድ ትስስር ይፈጥራል የተብሎ የታመነበት አፍሪካ ሶርሲንግ እና የፋሽን ሳምንት ለ10ኛ ጊዜ በአዲስአበባ ስካይላይት ሆቴል ከጥቅምት 23- 26  እንደሚካሄድ…
ተጨማሪ ያንብቡ
አምስት ‘አደገኛ’ ታራሚዎች ከቱኒዚያ እስርቤት አመለጡ 

አምስት ‘አደገኛ’ ታራሚዎች ከቱኒዚያ እስርቤት አመለጡ 

በቱኒዚያ ከሚገኝ እስር ቤትየተኒዚያ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ፎቶግራፋቸውን በማጋራት ዜጎች ራሳቸውን ከእነዚህ ግለሰቦች እንዲጠብቅና ማንኛውንም መረጃ እንዲሰጥ ጠይቋል።እስረኞቹ ማክሰኞ ማለዳ ከሞርናጊያ ማረሚያ ቤት አምልጠዋል ሲል ሚኒስቴሩ በፌስቡክ ገፁ ላይ አጋርቷል። በ2013 ሁለት ፖለቲከኞችን በመግደል ለእስር የተዳረገው አህመድ ማልኪ ካመለጡት መካከል አንዱ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል።እ.ኤ.አ. በ2013 የተፈፀመው ግድያ በቱኒዚያ የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ በማስከተል በወቅቱ በስልጣን ላይ የነበረው መንግስት ስልጣን እንዲለቅ አስገድዶታል።ካመለጡት እስረኞች መካከል ሬይድ ቱዋቲንም ያለበት ሲሆን የጸጥታ ምንጮች እንደሚሉት ባለፉት አስርት አመታት ቱኒዚያን ያንቀጠቀጠው እጅግ አስከፊ ጥቃት የመራ ሰው ስለመሆኑ ሮይተርስ ዘግቧል።ቱኒዚያ በ2011 የረዥም ጊዜ ገዢውን ዚን አል-አቢዲን ቤን አሊን ከስልጣን በማስወገድ የአረብ አብዮት መነሻ…
ተጨማሪ ያንብቡ
በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የተቋቋመው ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስት የሰዓት ገደብ ማሻሻያ ማድረጉን የጊዜአዊ ኮማንድ ፖስቱ አስታወቀ፡፡

በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የተቋቋመው ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስት የሰዓት ገደብ ማሻሻያ ማድረጉን የጊዜአዊ ኮማንድ ፖስቱ አስታወቀ፡፡

ጊዜአዊ ኮማንድ ፖስቱ "በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር እና በአካባቢው አሁናዊ የጸጥታ ሁኔታ አንጻራዊ መሻሻል እየመጣ በመሆኑ ህብረተሰቡ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን በተሻለ መልኩ ማከናወን እንዲችል የሰው፣ የባጃጅና ሆቴሎች  የስራ ሰዓት ማሻሻያ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።" ሲል ገልፆል። በዚህም መሠረት ከዛሬ ጥቅምት 21/ 2016 ዓ.ም ጀምሮ መንቀሳቀስ የሚቻለው ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት እስከ ምሽት 1:00 ሰዓት መሆኑን ኮማንድ ፖስቱ አሳውቋል።  ከዚህ ውጪ የተለየ እንቅስቃሴ በሚያደርግ ማንኛውም አካል  ላይ ኮማንድ ፖስቱ  በሚወስደው ህጋዊ እርምጃ ኃላፊነቱን የማይወስድ መሆኑን አክሎ አሳውቋል፡፡ መረጃውን ያገኘነው ከወልቂጤ ከተማ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት የፌስቡክ ገፅ ነው።
ተጨማሪ ያንብቡ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በማዕከላዊ ኢትዮጰያ ክልል ሥራዉን በይፋ ጀመረ።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በማዕከላዊ ኢትዮጰያ ክልል ሥራዉን በይፋ ጀመረ።

ኮሚሽኑ በክልሉ በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራትን   አስመልክቶ በሆሳዕና ከተማ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። የኮሚሽኑ  ኮሚሽነር  ዶክተር ዮናስ አዳዬ የክልሉ መንግስትና ህዝብ ለኮሚሽኑ ከወዲሁ እያሳየ ላለዉ ትብብር አመስግነዉ ይህም ለኮሚሽኑ አዎንታዊ ዉጤት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል። ኮሚሽነር ሙሉጌታ አጎ በበኩላቸው ኮሚሸኑ የተቋቋመበትን ህጋዊ መሠረት ጠቅሰዉ  በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከነገ ጀምሮ  በሆሳዕና ከተማ ለተባባሪ አካላት ሥልጠና እንደሚሰጥ ጠቁመዋል። ለሦሥት ተከታታይ ቀናት በሚቆየዉ ሥልጠና ከተለያዩ ማኅበራዊ መሠረት የተዉጣጡ የኅብረተሰብ ክፍሎች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል። በሥልጠናዉ የምክክር ጽንሰ-ሀሳብ፣ አላማ፣ ሂደት፣ አስቻይ ሁኔታዎችና ተግዳሮቶች የተመለከቱ   ርዕሰ-ጉዳዮች ይቀርባሉ ተብሏል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር  1265/2014 ተቋቁሞ ሥራ መጀመሩ ይታወቃል።  መረጃዉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኮሚንኬሽን…
ተጨማሪ ያንብቡ