አዲስ ጊዜ

228 Posts
መስከረም አበራ እና ቸርነት ፍቃዱ የተጣምሩበት “የፋሲካ ሌሊት” አዲስ ፊልም በቅርቡ ለእይታ ይበቃል ተባለ!

መስከረም አበራ እና ቸርነት ፍቃዱ የተጣምሩበት “የፋሲካ ሌሊት” አዲስ ፊልም በቅርቡ ለእይታ ይበቃል ተባለ!

በዳግም ሲሳይ ተጽፎና ዳይሬክት የተደረገው "የፋሲካ ሌሊት" አዲስ ፊልም በቅርቡ ለተመልካች ይቀርባል ተብሏል። ፊልሙ በሁለት የማይገናኙ ፍፁም ተቃራኒ የሆኑ ጥንዶች ባልታሰበ አጋጣሚ በፋሲካ ዋዜማ ሌሊት ተገናኝተው የሚያሳልፉትን የተለያዩ ክስተቶች የሚቃኝ ጭብጥ አለው፡፡ መስከረም አበራና ቸርነት ፍቃዱ ሙሉ ፊልሙ ላይ የሚታዩበት ሲሆን አስደናቂ ትወናቸውንም አሳይተውበታል፡፡ ቀረፃው በአዲስ አበባ አውራጎዳናዎች መንገድ በማዘጋትና በተለያዩ ቦታዎች የተሰራ ነው፡፡ በጀርመን ሀገር በተካሄደው European Work in Progress  ላይ በመሳተፍ፤ ከ250 በላይ በሚሆኑ የተለያዩ አለማቀፍ የፊልም ፈስቲቫል ተወካዮችና ፊልም አሰራጭ ድርጅቶች በተገኙበት ለእይታ ቀርቧል ተብሏል፡፡ ፊልሙ የአለማቀፍ ፌስቲቫሎች የጊዜ ሰሌዳ ካልተቀየር  በስተቀር በተያዝው አመት መጋቢት ወር ላይ በሀገር ውስጥ ሲኒማ ቤቶች ላይ የሚለቀቅ…
ተጨማሪ ያንብቡ
<<መንግሥት ለተፈናቃዮች ጥበቃ እና ድጋፍ የሚሰጥና የሚያስተባብር በግልጽ ሥልጣን የተሰጠው ተቋም በማቋቋም ወደ ሥራ ማስገባት ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ተግባር ነው።>> ኢሰመኮ

<<መንግሥት ለተፈናቃዮች ጥበቃ እና ድጋፍ የሚሰጥና የሚያስተባብር በግልጽ ሥልጣን የተሰጠው ተቋም በማቋቋም ወደ ሥራ ማስገባት ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ተግባር ነው።>> ኢሰመኮ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከሰኔ ወር 2014 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. ድረስ ያለውን ጊዜ የሚሸፍን ሁለተኛውን የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ባለ 60 ገጽ ሪፖርት ይፋ አድርጓል፡፡ ይህ ሁለተኛው የዘርፍ ሪፖርት ኢሰመኮ ሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ይፋ ካደረገው የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት ላይ በተጨማሪነት ኮሚሽኑ የተፈናቃዮች የሰብአዊ መብቶች አያያዝን በተመለከተ የለያቸውን መልካም ጅማሮዎች፣ አሳሳቢ ሁኔታዎችንና ምክረ ሐሳቦችን አካቷል። ኢሰመኮ በአፋር፣ አማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ኦሮሚያ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ፣ ማእከላዊ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና ሶማሊ ክልሎች በግጭት እና ሌሎች ሰው ሠራሽ መንሥዔዎች የተፈናቀሉ ከ369 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን፣ ተመላሾችን…
ተጨማሪ ያንብቡ
የዓለም የምግብ ፕሮግራም የአማራ ክልል ግጭት ለስራዬ እንቅፋት ሆኖብኛል አለ

የዓለም የምግብ ፕሮግራም የአማራ ክልል ግጭት ለስራዬ እንቅፋት ሆኖብኛል አለ

ጥቅምት 10/2016 ዓ.ም   የዓለም የምግብ ፕሮግራም ትናንት ጥቅምት 9 ቀን 2016 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ ለማቀርበው የምግብ እርዳታ የአማራ ክልል ግጭት እና የገንዘብ እጥረት ከፍተኛ ችግር ፈጥሮብኛል ሲል አስታወቀ። የዓለም የምግብ ፕሮግራም በአማራ ክልል በዘጠኝ ዞኖች በአሁኑ ወቅት በትጥቅ የተደገፈ ከፍተኛ ግጭት በመኖሩ እንቅስቃሴው መገደቡን እና በክልሉ የሚገኙ ሰራተኞቹን ደህንነት ለማስጠበቅ እንዲሁም ንብረቶቹ እንዳይዘረፉ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን  አስታውቋል። በተጨማሪም፣ እስከ አመቱ አጋማሽ ድረስ የረድኤት አቅርቦቱን በአግባቡ ለማከናወን ከሚያስፈልገው ገንዘብ ውስጥ 219 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር እጥረት እንደገጠመው የገለጸው ድርጅቱ በዚህም ሳቢያ በኢትዮጵያ የምግብ እርዳታ ከሚያስፈልጋቸው ውስጥ 50 በመቶ ለሚሆኑት ብቻ ለማቅረብ መገደዱን ጠቁሟል። እስከ ጥቅምት መጨረሻ ድረስ በኢትዮጵያ አስቸኳይ የምግብ…
ተጨማሪ ያንብቡ
በእገታ ስጋት ነዋሪዎች እየተፈናቀሉ ነው

በእገታ ስጋት ነዋሪዎች እየተፈናቀሉ ነው

ጥቅምት 10/2016   ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ ብቻ በኦሮሚያ ክልል ልዩ ልዩ አካባቢዎች በርካታ ሰዎች በታጣቂዎች እንደታገቱ የተለያዩ የዜና ምንጮች ዘግበዋል፡፡ አጋቾቹ የያዟቸውን ሰዎች ለመልቀቅ ከፍተኛ ገንዘብ እንደሚጠይቁ የተነገረ ሲኾን ከድርጊቱ መደጋገም የተነሣ ከፍተኛ ስጋት እንደገባቸው የገለጹ ነዋሪዎችም ቀዬአቸውን ለመልቀቅ እንደተገደዱ እየገለጹ ይገኛሉ፡፡ እገታ ከተፈጸመባቸው አካባቢዎች በአንዳቸው እንደተወለዱ የሚናገሩትና ስለኹኔታው እንደሚያውቁ የሚገልጹት አስተያየት ሰጪ፣ ሰሞኑን ስምንት አርሶ አደሮች በነፍስ ወከፍ እስከ 300ሺሕ ብር የማስለቀቂያ ዋስትና እንደከፈሉ ተናግረዋል፡፡ ከእገታው የተለቀቁ አንድ ግለሰብ ደግሞ፣ ነጻ ለመውጣት ከሌሎች ጓደኞቻቸው ጋራ ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ከፍለናል ሲሉ ለዜና ማሰራጫዎች ተናግረዋል፡፡ የኦሮሚያ ክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ ኃይሉ አዱኛ፣ መንግሥት ኦነግ…
ተጨማሪ ያንብቡ
22 ጋዜጠኞች መሞታቸው ተነገረ

22 ጋዜጠኞች መሞታቸው ተነገረ

ጥቅምት 10/2016   ሲፒጄ የእስራኤል እና ሐማስ ግጭት ከጀመረ አንስቶ ቢያንስ 22 ጋዜጠኞች ተገድለዋል አለ። የጋዜጠኞች መብት ተቆርቋሪ ድርጅቱ (ሲፒጄ) ባለፉት ሁለት ሳምንታት ከተገደሉት ጋዜጠኞች መካከል 18ቱ ፍልስጤማውያን ናቸው ብሏል። የሲፒጄ መግለጫ እንደሚያብራራው 15 ጋዜጠኞች ሕይወታቸውን ያጡት በእስራኤል የአየር ጥቃት ሲሆን ሁለት ጋዜጠኞች ደግሞ በደቡባዊ እስራኤል በሐማስ ጥቃት የተገደሉ ናቸው። ቡድኑ በመግለጫው 8 ጋዜጠኞች ጉዳት እንደደረሰባቸው የገለጸ ሲሆን ሦስት ጋዜጠኞች የደረሱበት እንደማይታወቅ ምናልባትም በእስር ላይ ሊሆኑ ይችላሉ ብሏል። ሲፒጄ ጋዜጠኝነት ሰላማዊ እንቅስቃሴ መሆኑን በመግለጽ ታጣቂዎች ሞያውንና ባለሞያዎቹን ዒላማ ከማድረግ እንዲቆጠቡ አሳስቧል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
በክልሉ የቀጠለው ግጭት ፈተና እንደሆነባቸው የአማራ ተማሪዎች ገለጹ

በክልሉ የቀጠለው ግጭት ፈተና እንደሆነባቸው የአማራ ተማሪዎች ገለጹ

ጥቅምት 10/2016 በአማራ ክልል ከጊዜ ወደጊዜ እየተስፋፋ በመጣው ግጭት ምክንያት የትራንስፖርት አገልግሎት በመስተጓጎሉ በክልሉ የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ወደየሚማሩባቸው ዩኒቨርሲቲዎች መመለስ እንዳልቻሉ ተናገሩ፡፡ በሲዳማ ክልል በሚገኘው ሀዋሳ እንዲሁም በዲላ ዩኒቨርሲቲዎች እንዳሉ የገለጹት ተማሪዎች፣ ከሚኖሩባቸው አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባም ኾነ የአውሮፕላን በረራ ወዳለባቸው ከተሞች ለመሔድ እንደተቸገሩ ለቪኦኤ የዜና ማሰራጫ ገልጸዋል፡፡ ሌሎች ተማሪዎች ደግሞ፣ ከክልሉ ወደ አዲስ አበባ የየብስ ትራንስፖርት ማግኘት ባለመቻላቸው፣ ሦስት እጥፍ በኾነ ወጪ ከአካባቢዎቹ በአውሮፕላን ለመውጣት እንደተገደዱ ጠቅሰው፣ መንግሥት ወደየሚማሩባቸው ዩኒቨርሲቲዎች እንዲያደርሳቸው ጠይቀዋል፡፡ በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ የዩኒቨርሲቲዎቹ አመራሮች በበኩላቸው፣ የዐማራ ክልል ተማሪዎቻቸውን በከፊል እየተቀበሉ እንደሚገኙ አስታውቀዋል፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር ደግሞ፣ “ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተልኩ ነው፤…
ተጨማሪ ያንብቡ
መከላከያ በ“ሸኔ ቡድን” ላይ ወሰድኩት ባለው እርምጃ ዋና አመራሩን ገድያለሁ አለ

መከላከያ በ“ሸኔ ቡድን” ላይ ወሰድኩት ባለው እርምጃ ዋና አመራሩን ገድያለሁ አለ

ጥቅምት 10/2016 ዓ.ም   በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን መንግስት “ሸኔ” ብሎ በሚጠራው ኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ታጣቂዎች ላይ በወሰደው እርምጃ የቡድኑ ከፍተኛ አመራር የሆነው ጃል ቦሩ አምቦን እና ሌሎች በርካታ የቡድኑ አባላትን መግደሉን አስታወቀ። መከላከያ ሰራዊቱ በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ ጥቅምት 9 ቀን 2016 ዓ.ም ባሰፈረው ሀተታ በአካባቢው የሚገኘው የመከላከያ ሠራዊት አባላት በምዕራብ ሽዋ ዞን በአቡና ግንደ በረት ወረዳ ፋጅና ጌርጌራ በተባሉ አካባቢዎች ላይ ጥቃት የሰነዘረው ታጣቂ ቡድንን መደምሰሱን አስታውቋል። መከላከያ በዚህ መግለጫው ቡድኑ ሲጠቀምባቸው የነበሩ የተለያዩ የነፍስ ወከፍ መሣሪያዎችን እና ተተኳሾችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ሻምበል እንግዳሸት መከተን ጠቅሶ መረጃውን አስፍሯል። በተመሳሳይ በጀልዱ ወረዳ በጩልቄ እና በሽኩቴ…
ተጨማሪ ያንብቡ
ካቻ “የግልየክፍያሰነድአዉጪ” በመሆን በሙሉ አቅሙ ሥራ መጀመሩን አስታወቀ

ካቻ “የግልየክፍያሰነድአዉጪ” በመሆን በሙሉ አቅሙ ሥራ መጀመሩን አስታወቀ

ቅዳሜ ጥቅምት 10 ቀን 2016 በኢትዮጵያ የዲጅታል ፋይናንስ አገልግሎት ላይ የተሰማራው ካቻ ዲጂታል የፋይናንስ አገልግሎት አክሲዮን ማሕበር፤ በአገሪቱ የመጀመሪያው "የግል የክፍያ ሰነድ አዉጪ" በመሆን በሙሉ አቅሙ ሥራ መጀመሩን ትናንት ሐሙስ ምሽት ጥቅምት 8/2016 በስካይላይት ሆቴል በነበረው መርሃ ግብር ላይ አብስሯል። በዚህም መሰረት የሞባይል የገንዘብ ዝውውር አገልግሎትን ጨምሮ የተለያዩ የክፍያ ሰነዶችን ለማውጣት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፍቃድ ያገኘ የመጀመርያው የግል የክፍያ ሰነድ አውጪ መሆን ችሏል። ካቻ ከአለም አቀፍ ሐዋላ አስተላላፊዎች ጋር በፈጠረው አጋርነት ደህንነቱ የተጠበቀ የውጪ ሐዋላን በማሳለጥ፤ ላኪዎችም ሆኑ ተቀባዮች ተጨማሪ የፋይናንስ አገልግሎቶች ዕድል የሚያገኙበት አሰራር መዘርጋቱን ገልጿል። ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነ የአሰራር ስርዓት ዓለም አቀፍ የሐዋላ…
ተጨማሪ ያንብቡ
ሥራ አጥነት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ችግር እንደሆነ መንግሥት አመነ

ሥራ አጥነት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ችግር እንደሆነ መንግሥት አመነ

ቅዳሜ ጥቅምት 10/2016 በኢትዮጵያ፣ ሥራ አጥነት እጅግ አሳሳቢ ብሔራዊ ችግር ከኾነበት ደረጃ ላይ እንደደረሰ የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሡ ጥላሁን በአዲስ አበባ የተዘጋጀውን ሀገር አቀፍ የሥራ ዐውደ ርእይ ሲከፍቱ ባሰሙት ንግግር፣ ሥራ አጥነት የችግሮች ሁሉ አውራ እንደኾነ ገልጸው፣ መፍትሔው የሁሉንም ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል። ባሳለፍነው ረቡዕ የተከፈተው ዐውደ ርእይ፣ ከ20ሺሕ በላይ አዲስ ተመራቂ ሥራ ፈላጊዎችንና 200 ቀጣሪ ድርጅቶችን እንደሚያገናኝ ተነግሮለታል። ልዩ ልዩ አካላት በትብብር እንዳዘጋጁት የተነገረለት ይኸው ሀገር አቀፍ የሥራ ዐውደ ርእይ፣ ለስድስት ሺሕ አዲስ ተመራቂዎች፣ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ተመልክቷል፡፡ በዝግጅቱ የተሳተፈው ዳሽን ባንክ፣ በሁለት ቀኑ የሥራ ዐውደ ርእይ፣ ሦስት…
ተጨማሪ ያንብቡ
የሱዳንን ቀውስ ለመፍታት በአዲስ አበባ ጉባዔ ተዘጋጀ

የሱዳንን ቀውስ ለመፍታት በአዲስ አበባ ጉባዔ ተዘጋጀ

ቅዳሜ ጥቅምት 10/2016 በጎረቤት ሱዳን የተፈጠረውን ቀውስ ለመፍታት ያለመ እና የሱዳን ሲቪል ተቋማት የሚሳተፉበት ጉባዔ ከዛሬ ጥቅምት 10 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለአራት ቀናት በአዲስ አበባ እንደሚያካሄድ ተገለጸ። የሱዳን ሲቪል ሀይሎች በአዲስ አበባ በሚያካሂዱት በዚህ ጉባዔ ዋነኛ ትኩረት የሚሆነው በሀገሪቱ ለስድስት ወራት የዘለቀውን ግጭት እልባት ለመስጠት የሚያስችል ስልት መቀየስ መሆኑን ታማዙጂ ራዲዮ በድረገጹ ላይ በሰራው ዘገባ ጠቁሟል። በሳምንቱ መጨረሻ በአዲስ አበባ የሚደረገውን ጉባዔ ለማሳለጥ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን ከተሳታፊዎች አንዱ የሆነው ኡማ ፓርቲ የሚዲያ ሃላፊ ሚስባህ አህመድ መሃመድ አረጋግጠዋል። ጉባዔው ከ70 በላይ የሚሆኑ የተለያዩ የሱዳን ሲቪል ተቋማትን እና ማህበረሰብ አንቂዎችን ተሳታፊ እንደሚያደርግ ተጠቁሟል።   የጉባዔው ዋነኛ ግብ በቀጣይ ወር…
ተጨማሪ ያንብቡ