አዲስ ጊዜ

230 Posts
ሥራ አጥነት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ችግር እንደሆነ መንግሥት አመነ

ሥራ አጥነት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ችግር እንደሆነ መንግሥት አመነ

ቅዳሜ ጥቅምት 10/2016 በኢትዮጵያ፣ ሥራ አጥነት እጅግ አሳሳቢ ብሔራዊ ችግር ከኾነበት ደረጃ ላይ እንደደረሰ የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሡ ጥላሁን በአዲስ አበባ የተዘጋጀውን ሀገር አቀፍ የሥራ ዐውደ ርእይ ሲከፍቱ ባሰሙት ንግግር፣ ሥራ አጥነት የችግሮች ሁሉ አውራ እንደኾነ ገልጸው፣ መፍትሔው የሁሉንም ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል። ባሳለፍነው ረቡዕ የተከፈተው ዐውደ ርእይ፣ ከ20ሺሕ በላይ አዲስ ተመራቂ ሥራ ፈላጊዎችንና 200 ቀጣሪ ድርጅቶችን እንደሚያገናኝ ተነግሮለታል። ልዩ ልዩ አካላት በትብብር እንዳዘጋጁት የተነገረለት ይኸው ሀገር አቀፍ የሥራ ዐውደ ርእይ፣ ለስድስት ሺሕ አዲስ ተመራቂዎች፣ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ተመልክቷል፡፡ በዝግጅቱ የተሳተፈው ዳሽን ባንክ፣ በሁለት ቀኑ የሥራ ዐውደ ርእይ፣ ሦስት…
ተጨማሪ ያንብቡ
የሱዳንን ቀውስ ለመፍታት በአዲስ አበባ ጉባዔ ተዘጋጀ

የሱዳንን ቀውስ ለመፍታት በአዲስ አበባ ጉባዔ ተዘጋጀ

ቅዳሜ ጥቅምት 10/2016 በጎረቤት ሱዳን የተፈጠረውን ቀውስ ለመፍታት ያለመ እና የሱዳን ሲቪል ተቋማት የሚሳተፉበት ጉባዔ ከዛሬ ጥቅምት 10 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለአራት ቀናት በአዲስ አበባ እንደሚያካሄድ ተገለጸ። የሱዳን ሲቪል ሀይሎች በአዲስ አበባ በሚያካሂዱት በዚህ ጉባዔ ዋነኛ ትኩረት የሚሆነው በሀገሪቱ ለስድስት ወራት የዘለቀውን ግጭት እልባት ለመስጠት የሚያስችል ስልት መቀየስ መሆኑን ታማዙጂ ራዲዮ በድረገጹ ላይ በሰራው ዘገባ ጠቁሟል። በሳምንቱ መጨረሻ በአዲስ አበባ የሚደረገውን ጉባዔ ለማሳለጥ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን ከተሳታፊዎች አንዱ የሆነው ኡማ ፓርቲ የሚዲያ ሃላፊ ሚስባህ አህመድ መሃመድ አረጋግጠዋል። ጉባዔው ከ70 በላይ የሚሆኑ የተለያዩ የሱዳን ሲቪል ተቋማትን እና ማህበረሰብ አንቂዎችን ተሳታፊ እንደሚያደርግ ተጠቁሟል።   የጉባዔው ዋነኛ ግብ በቀጣይ ወር…
ተጨማሪ ያንብቡ
ቦሌ የሚገኘው ፉድ ዞን ሬስቶራንት የእሳት አደጋ ደረሰበት

ቦሌ የሚገኘው ፉድ ዞን ሬስቶራንት የእሳት አደጋ ደረሰበት

አርብ ጥቅምት 09/2016 በአሸናፊ አሰበ ቦሌ ክፍለከተማ ወረዳ6 ልዩ ስሙ ብራስ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘው ፉድ ዞን ሬስቶራንት ሀሙስ ምሽት 4 ሰዓት ከ40 ላይ ኩሽና ውስጥ ከመጥበሻ ላይ ተነሳ በተባለ እሳት ጉዳት እንደደረሰበት የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ንጋቱ ማሞ ለአዲስ ጊዜ ገልጸዋል፡፡ በአደጋው ከ1.5 ሚሊየን ብር በላይ የንብረት ውድመት የደረሰ ሲሆን 1 ሰዓት 30 በፈጀ ርብርብ እሳቱን ወደሌላ ቦታ ሳይዛመት ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ውስጥ ለማዋል መቻሉን ሃላፊው ጨምረው ገልጸዋል፡፡ አደጋውን ለመቆጣጠር 25 የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች እና 4 የእሳት አደጋ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት ላይ የዋሉ ሲሆን ከ11 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት…
ተጨማሪ ያንብቡ
በጎጃም ቡሬ ከተማ አቅራቢያ ግጭት መኖሩ ተነገረ

በጎጃም ቡሬ ከተማ አቅራቢያ ግጭት መኖሩ ተነገረ

ሐሙስ ጥቅምት 08/2016 ካለፈው ሐምሌ ወር 2016 ዓ.ም ጀምሮ በአማራ ክልል እየሰፋ የመጣው ግጭት በተለይ በጎጃም አንዳንድ አካባቢዎች አሁንም መቀጠሉን አዲስ ጊዜ ያነጋገረቻቸው ነዋሪዎች ገልፀዋል፡፡ አንፃራዊ ሰላም ካለባቸው ከተሞች ውጭ በመከላከያ ሰራዊቱ እና በፋኖ ታጣቂ ቡድን መካከል ያለው ግጭት አሁንም በበርካታ የገጠር ቀበሌዎች መኖሩን እኚሁ ነዋሪዎች አረጋግጠውልናል፡፡ ሰዓት እየጠበቁ የሚሰሙት የከባድ መሳሪያ የተኩስ ድምፆች የረጋ ሕይወት  እንዳይኖራቸው ምክንያት መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡ ምስክርነታቸውን ለአዲስ ጊዜ የሰጡት፣ በምዕራብ ጎጃም ዞን የቡሬ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ "ቡሬ ከተማ ላይ ጊዜያዊ ሰላም ቢኖርም ትናንት ከከተማው በቅርብ ርቀት ላይ ከምትገኝ ሸንዲ ከተማ አጠገብ ካለው ሰባ አዳር የሚባል አካባቢ ዙርያ ከባድ የተኩስ…
ተጨማሪ ያንብቡ
የሾኔ ሆስፒታል በስራ ማቆም አድማ ምክንያት አገልግሎት መስጠት አቋረጠ

የሾኔ ሆስፒታል በስራ ማቆም አድማ ምክንያት አገልግሎት መስጠት አቋረጠ

ሐሙስ 08/2016 በሀዲያ ዞን በምትገኘው ሾኔ ከተማ ውስጥ የህክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሙሉ በሙሉ ስራ ማቋረጡን ከአካባቢው የተገኘው መረጃ አመላክቷል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ላለፉት ሶስት ወራት ደመወዝ አልተከፈለንም ያሉ ሰራተኞች ባነሱት የስራ ማቆም አድማ መነሻነት መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል፡፡ የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ተድላ አካሉ በሾኔ ከተማ ውስጥ የሚገኘው ይህ ሆስፒታል ስራ ማቆሙን አምነው አገልግሎት መስጠት ካቆመ አንድ ሳምንት ማስቆጠሩን ጨምረው አስታውቀዋል፡፡ ይህን የዶክተር ተድላ ሀሳብ የተጋሩት የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ መለሰ ተሰማ ዝርዝር መረጃ ለመስጠት ግን እንደተቆጠቡ ቪኦኤ የዜና ማሰራጫ በዘገባው አብራርቷል፡፡ ይህ አጋጣሚ የመጀመሪያቸው እንዳልሆነ የሚናገሩትና በባለሞያነት ሲያገለግሉ የቆዩት የተቋሙ ሰራተኞች፣ ከዚህ…
ተጨማሪ ያንብቡ
የ12ኛ ክፍል ውጤት እኛንም አስገርሞናል-ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

የ12ኛ ክፍል ውጤት እኛንም አስገርሞናል-ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

ጥቅምት 07/2016 የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ዶር) ዛሬ በርላማ ተገኝተው ከሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ለሚኒስትሩ ከቀረቡላቸው ጥያቄዎች መካከል የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤትን የሚመለከተው ይገኝበታል። የቋሚ ኮሚቴውን ጥያቄዎች በንባብ ያሰሙት የፓርላማ አባል “በተከታታይ ለሁለት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤት በጣም ዝቅተኛ የሆነበት ምክንያት ምንድነው? ትምህርት ሚኒስቴር የፈተናውን ውጤት እንዴት ያየዋል?” ሲሉ ጠይቀዋል። ፕ/ር ብርሃኑ ለዚህ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ “የ12ኛ ክፍል ውጤት እንደዚህ መሆን ሁላችንንም አስገርሞናል” ብለዋል። “የፈተናውን አሰጣጥ መቀየር ብቻ ይሄን ካሳየ፤ ከዚህ ተነስተን ብቸኛ ነገር ልንል የምንችለው፤ ከዚያ በፊት ስንሰጣቸው…
ተጨማሪ ያንብቡ
የሰላም እጦት ለሱሰኛ ቁጥር መጨመር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል ተባለ

የሰላም እጦት ለሱሰኛ ቁጥር መጨመር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል ተባለ

ጥቅምት 07/2016 በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ እየታየ ያለው የሰላም እጦት እና የስራ አጥነት ቁጥር መጨመር በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ ለመጣው የሱስ ተጠቂዎች ቁጥር ሚናው የጎላ እንደሆነ በአማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአእምሮ ህክምና ስፔሻሊስት የሆኑት አስራት ጫካ ለአዲስ ጊዜተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የሚስተዋለው የፖለቲካ አለመረጋጋት ለሚሊዮኖች መፈናቀል እና ሞት ምክንያት ሲሆን፣ ቁጥራቸው የማይገመት ህጻናትንም ቤተሰብ አልባ አድርጓል፡፡ በኢትዮጵያ ከ 5.5 ሚሊየን የሚልቁ ህጻናት ወላጅ አልባ እንደሆኑ የዩኒሴፍ ዘገባ የሚያመላክት ሲሆን ይህም ህጻናቱን ለሱስ የሚኖራቸውን ተጋላጭነት ከፍ እንደሚያደርገው ይታመናል። ጦርነት፣ የፖለቲካ አለመረጋጋት፣ መፈናቀል እና ድርቅ ለሱስ አጋላጭነት ቀላል የማይባል ሚና እንደሚጫወቱ ሱስ ላይ የተሰሩ ልዩ ልዩ ጥናታዊ ጽሁፎች ያስረዳሉ፡፡ በኢትዮጵያ ሰፊ ሽፋን…
ተጨማሪ ያንብቡ
ከሱዳን 38ሺህ ኢትዮጵያውያን ድንበር አቋርጠው ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸው ተገለፀ

ከሱዳን 38ሺህ ኢትዮጵያውያን ድንበር አቋርጠው ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸው ተገለፀ

ጥቅምት 07/2016 በሚያዝያ ወር 2015 ዓ.ም የሱዳን ተፋላሚ ሀይሎችን ግጭት በመሸሽ 38ሺህ 560 የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን ድንበር አቋርጠው ወደ ሀገራቸው መግባታቸውን አለምዓቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) አስታወቀ፡፡ ስድስተኛ ወሩን ከተሻገረው እጅግ ደም አፋሳሽ ከሆነው ከዚህ ጦርነት ራሳቸውን ለማዳን ወደ ኢትዮጵያ የገቡ አጠቃላይ ስደተኞች ቁጥር 85ሺህ 600 መሻገሩን ድርጅቱ ያወጣው ዝርዝር መግለጫ ያመለክታል፡፡ ከዚህ መካከል 30ሺህ 560 ያህሉ ኢትዮጵያን ሲሆኑ 31ሺህ 115 የሚሆኑት ደግሞ ሱዳናውያን ስለመሆናቸው ተነግሯል፡፡ የተቀሩት 15ሺህ 821ዱ ደግሞ የሶስተኛ ሀገራት ዜጎች ናቸው፡፡ ከፊሎቹ ወደ ሌሎች ሀገራት መሻገራቸውን የፍልሰተኞች ድርጅት መረጃ ጠቁሟል:: አጠቃላይ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡት ከ85ሺህ በላይ ስደተኞች መካከል 35ሺህ 440 የሚሆኑት ሴቶች ሲሆኑ 50ሺህ 56…
ተጨማሪ ያንብቡ
የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎትከፍተኛ አመራሮች መታሰራቸው ተሰማ

የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎትከፍተኛ አመራሮች መታሰራቸው ተሰማ

ጥቅምት 07/2016 የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ታምሩ ገምበታን ጨምሮ በቁጥር ለጊዜው ያልታወቁ ሰዎች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው መታሰራቸው ተሰማ። ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ሰሞኑን ሲሆን አቶ ታምሩ ገምበታ ግን ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. መሆኑ ተገልጿል። የምክትል ዳይሬክተሩ ቤት በፍርድ ቤት የብርበራ ፈቃድ መፈተሹንና ዛሬ ጥቅምት 7 ቀን 2015 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ሊቀርቡ እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡ የመንግሥት አስተዳደር ለውጥ ከተደረገ ጀምሮ የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ተቋም ውስጥ የተለያዩ ለውጦች (ሪፎርም) የተደረገ ቢሆንም፣ አንዳንድ የተቋሙ ሠራተኞች በድለላ ሥራ ከተሰማሩ አካላት ጋር በመመሳጠር የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል ተብለው በቁጥጥር ሥር ውለው በምርመራ ላይ እንዳሉ ይታወቃል። አገልግሎቱን…
ተጨማሪ ያንብቡ
የሶማሊያው አውዳል ራስ ገዝ ግዛት የኢትዮጵያን የወደብ ጥያቄ እንደሚቀበል ገለፀ

የሶማሊያው አውዳል ራስ ገዝ ግዛት የኢትዮጵያን የወደብ ጥያቄ እንደሚቀበል ገለፀ

ጥቅምት 07/2016 (ቀይ ባሕር) ከሱማሊላንድ በመነጠል ከሀገረ ሶማሊያ ጋር አንድነት ለመፍጠር እየታገለ ያለው የአውዳል ግዛት ንቅናቄ፣ ኢትዮጵያ በዘይላ ወደብ በኩል ወደ ቀይ ባህር ለመቅረብ ፍላጎት ካላት ሙሉ ትብብር እንደሚያደርግ ገለጸ፡፡ ንቅናቅው ትናንት ባወጣው ዝርዝር መግለጫ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ከሰሞኑ የሰጡትን ማብራርያ እንዳጤነው ዘርዝሮ “ይህን ህልማቸውን ለማሳካት  በይፋ ግብዣ አቀርባለው” ሲል የጠቅላይ ሚንስትሩ ሀሳብ ተጋሪ መሆኑን አረጋግጧል፡፡ የአውዳል ግዛት ንቅናቄ፣ ታሪካዊው የዘይላ ወደብ ለኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ክፍት እንደሚሆን እና ይህም በመግባቢያ ሰነድ እንደሚፀና በጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አብራርŸል፡፡ ጨምሮም ይህ  ሂደት ሁሉንም ወገን አሸናፊ ያደርጋል ሲል ደምድሟል፡፡ ይህ የአውዳል ግዛት ንቅናቄ መግለጫ በሶማሊያውያን ዘንድ መነጋገርያ እየሆነ…
ተጨማሪ ያንብቡ