ያገባኛል

በአማራ ክልል ለተፈጠረው ግጭት ዘላቂ በቂ መፍትሔ ባለመሰጠቱ ምክንያት ከፍተኛ የሆኑ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች እየተፈጸሙ ይገኛሉ፡፡ኢሰመጉ

በአማራ ክልል ለተፈጠረው ግጭት ዘላቂ በቂ መፍትሔ ባለመሰጠቱ ምክንያት ከፍተኛ የሆኑ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች እየተፈጸሙ ይገኛሉ፡፡ኢሰመጉ

እታገኘሁ መኮነን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ(ኢሰመጉ) ህዳር07/2016“ በአማራ ክልል እየጨመረ የመጣው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ኢሰመጉን በእጅጉ ያሳስቡታል! ” በሚል ባወጣው መግለጫ በአማራ ክልል ለተፈጠረው ግጭት  ዘላቂ የሆነ በቂ መፍትሔ ባለመሰጠቱ ምክንያት ከፍተኛ የሆኑ የሰብዓዊ የመብት ጥሰቶች እየተፈጸሙ ይገኛሉ ብሏል፡፡ ኢሰመጉ በአማራ ክልል ውስጥ ያለውን ግጭት አስመልክቶ ለግጭቱ መነሻ የሆኑ ምክንያቶች መታየት ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ በተደጋጋሚ መግለጫዎችን በማውጣት ይህ አለመግባባት ለከፋ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ምክንያት እንዳይሆን ሲያሳስብ እና ሲወተውት ቢቆይም ከመንግስት በኩል ለኢሰመጉ ምክረ ኃሳቦች በቂ ትኩረት ባለመሰጠቱ እና ለግጭቱ ዘላቂ መፍትሔ ባለመቅረቡ ምክንያት መጠነ ሰፊ የሆኑ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች በክልሉ እንዲፈጸሙ ምክንያት ሆኗል ብሏል፡፡ በአማራ ክልል…
ተጨማሪ ያንብቡ
ኢሰመኮ ዓለም አቀፍ ለጋሽ ድርጅቶች እርዳታ ለመቀጠል መወሰናቸውን አደነቀ

ኢሰመኮ ዓለም አቀፍ ለጋሽ ድርጅቶች እርዳታ ለመቀጠል መወሰናቸውን አደነቀ

ዳዊት ታደሰ የኢትዮጵያ ሰበአዊ መብቶች ኮሚሽን ህዳር 07 ቀን 2016 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ የአሜሪካ መንግስት የዓለም አቀፍ ልማት ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስ ኤድ) እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዓለም የምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ አቋርጠውት የነበረውን የምግብ እርዳታ መልሰው ለመጀመር መወሰናቸው የሚወደስ ነው ብሏል፡፡ ኢሰመኮ በመግለጫው፣ በትግራይ ክልል ከባለፈው ዓመት መጋቢት ወር ጀምሮ በኢትዮጵያ ደረጃ ደግሞ ከሰኔ ወር ጀምሮ የተቋረጠውን የምግብ እህል እርዳታ ተከትሎ ስለተፈጠረው ሁኔታ ክትትል ሲያደርግ እንደነበር ዘርዝሯል፡፡ ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ፍልሰተኞች በተለይ ደግሞ ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ ህጻናት ጋር ለመድረስ እንዲቻል አስተዳደራዊ እርምጃዎችን ጨምሮ ሌሎች የማስተባበር ስራዎች በፍጥነት እንዲከወኑ ሲወተውት መቆየቱን ያስታወሰው ኮሚሽኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት…
ተጨማሪ ያንብቡ
ስደተኞችን በማስጠለል ከአፍሪካ ቀዳሚ የነበረችው ኢትዮጵያ በ3ኛነት                       ተቀመጠች::

ስደተኞችን በማስጠለል ከአፍሪካ ቀዳሚ የነበረችው ኢትዮጵያ በ3ኛነት ተቀመጠች::

ለበርካታ ዓመታት በአፍሪካ በአንደኝነት ደረጃ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ስደተኛ አስጠልላ የቆየችው ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ሶስተኛዋ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ስደተኛ ተጠልሎባት የሚገኝ ሀገር ናት ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታወቀ። ሱዳንን እና ኡጋንዳን በመከተል በሶስተኝነት ስደተኞችን ያስጠለለችው ኢትዮጵያ 954ሺ ከተለያዩ ሀገራት ድንበሯን አቋርጠው የገቡ ስደተኞች እንደሚገኙባት ተቋሙ ይፋ ባደረገው መረጃ ጠቁሟል። የመንግስታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት ዩኤንኤችሲአር ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያመላክተው በኢትዮጵያ ተጠልለው ከሚገኙ ስደተኞች መካከል ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዙት ሱዳናውያን ናቸው። ከሶማሊያ እና ከኤርትራ ተሰደው በኢትዮጵያ የተጠለሉ ስደተኞች በሁለተኝነት እና በሶስተኝነት ተቀምጠዋል። ኢትዮጵያ በሁሉም ድንበሮቿ የጎረቤት ሀገራት ስደተኞች እንዲገቡ በሮቿን ክፍት ማድረጓን የጠቆመው የመንግስታቱ…
ተጨማሪ ያንብቡ
የአየር ንብረት ለውጥ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተነገረ

የአየር ንብረት ለውጥ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተነገረ

በዘላቂ የልማት ግቦች እና በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የሚያጠነጥን የግማሽ ቀን አውደ-ጥናት ትናንት ጥቅምት 20 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ መካሄዱን አዲስ ጊዜ አይታለች፡፡ ኤንዳ ኢትዮጵያ በመባል በሚታወቀው እና በዋናነት በከተማ ልማት እንዲሁም በአካባቢያዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን አድርጎ በሚሰራው መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት አስተባባሪነት በተዘጋጀው በዚህ መርሀ-ግብር ላይ ጥናታዊ ጽሑፎች የቀረቡ ሲሆን በተለያዩ የዜና ማሰራጫ ተቋማት ውስጥ የሚሰሩ የመገናኛ ብዙሐን ባለሞያዎችም የውይይቱ አካል ነበሩ፡፡ የአየር ንብረት ለውጥ ምልክቶች እና እያስከተሉ ያሉት መጠነ ሰፊ ጉዳቶች በአውደ-ጥናቱ ላይ በዝርዝር ቀርበዋል፡፡ በተለይ፣ ችግሩ ከኢትዮጵያ አንጻር የተዳሰሰበት ክፍል በተሳታፊዎች ዘንድ መነጋገሪያ እንደነበር መታዘብ ተችሏል፡፡ እ.አ.አ በ2030 ዓ.ም ይሳካሉ ተብለው ግብ የተያዘላቸው…
ተጨማሪ ያንብቡ
“ሜታ በትግራይ ተወላጆች ላይ ለሚደርሰው ከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰት አስተዋጽኦ አድርጓል” አምነስቲ ኢንተርናሽናል

“ሜታ በትግራይ ተወላጆች ላይ ለሚደርሰው ከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰት አስተዋጽኦ አድርጓል” አምነስቲ ኢንተርናሽናል

በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅት የትግራይ ተወላጆች ላይ በማነጣጠር ለተሰነዘሩ ማንነት ተኮር ጥቃቶች የፌስቡክ እናት ኩባንያ የሆነው ሜታ ተባባሪ ሆኗል ሲል የአለም ዓቀፉ የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ወቀሰ፡፡ አምነስቲ ትናንት ጥቅምት 20/2016 ይፋ ባደረገው ሪፖርቱ "ሜታ በሰሜን ኢትዮጵያ ለሚፈጸሙ የሰብአዊ መብት ረገጣዎች ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል" ያለ ሲሆን፤ ኩባንያው ጥላቻ እና ጥቃትን የሚያበረታቱ ይዘቶችን በበቂ ሁኔታ መቆጣጠርና መግታት አለመቻሉን ገልጿል፡፡ በዚህም “ፌስቡክ የሚከተለው ደካማ የንግድ ሞዴል እና መረጃዎችን የመቆጣጠር እንቅስቃሴ፤ በትግራይ ተወላጆች ላይ ያነጣጠሩ የጥላቻ እና የቅስቀሳ ዘመቻዎችን እንዳይቆጣጠር አድርጎታል” ያለ ሲሆን፤ ከዚህም ጋር ተያይዞ በሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት ወቅት በትግራይ ማህበረሰብ ላይ ለደረሰው ግፍ ኩባንያው የራሱን…
ተጨማሪ ያንብቡ
የአማራ ክልል ሁሉም ዞኖች በተለያየ ደረጃና ጊዜ የትጥቅ ግጭት ተካሂዶባቸዋል ተባለ።

የአማራ ክልል ሁሉም ዞኖች በተለያየ ደረጃና ጊዜ የትጥቅ ግጭት ተካሂዶባቸዋል ተባለ።

ሰኞ ጥቅምት 19/2016 የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የአማራ ክልልን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ዛሬ ባሰራጨው ዘለግ ያለ ዘገባ ከ ሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም አንስቶ ባሉት ጊዜያት በአማራ  ክልል ሁሉም ዞኖች በተለያየ ደረጃና ጊዜ የትጥቅ ግጭት ተካሂዶባቸዋል ሲል ገልጿል። በተጨማሪም እነዚህ አካባቢዎች ወይም ወረዳዎች በአንድ ወቅት በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች፣ በሌላ ወቅት በታጣቂው ቡድን (በተለምዶ ፋኖ በመባል የሚታወቀው) ቁጥጥር ሥር ውለዋል። የትጥቅ ግጭቱ በአንዳንድ አካባቢዎች በከባድ መሣሪያ እና አልፎ አልፎ በአየር/ድሮን ድብደባ ጭምር የታገዘ ነው ሲል ገልጿል። በግጭቱ ዐውድ የአየር/ድሮን መሣሪያን ጨምሮ በከባድ መሣሪያዎች ጥቃት የተነሳ በሲቪል ሰዎች ላይ ሞት እና የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን፣ ሰዎች መኖሪያ አካባቢያቸውን ጥለው…
ተጨማሪ ያንብቡ
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም. የኮሚሽኑን 2ኛ ዓመታዊ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መብቶችን ሁኔታ በተመለከተ ያወጣውን መግለጫ በተመለከተኢሰመኮመግለጫአውጥቷል፡፡

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም. የኮሚሽኑን 2ኛ ዓመታዊ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መብቶችን ሁኔታ በተመለከተ ያወጣውን መግለጫ በተመለከተኢሰመኮመግለጫአውጥቷል፡፡

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጋዜጣዊ መግለጫ ጥቅምት 16 ቀን 2016 ዓ.ም.  የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ/ኮሚሽኑ) ጥቅምት 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፋ ያደረገውን ሁለተኛውን የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መብቶች ሁኔታ ሪፖርት በሚመለከት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ የኮሚሽኑ ሪፖርት በጦርነት ምክንያት ተፈናቅለው የነበሩ የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች በብዛት ወደ መኖሪያ አካባቢያቸው እንደተመለሱ እና ሰብአዊ ድጋፍ እየቀረበላቸው እንደሆነተደርጎ የተገለጸው ስሕተት ስለሆነ ሊስተካከል ይገባል በሚል መግለጹን ተከትሎ፣ ኢሰመኮ ወዲያውኑ በሰጠው አጭር ማብራሪያ ሪፖርቱ ይህንን መሰል መረጃ እንደማያካትት፣ የሪፖርቱ አካባቢያዊ ወሰን የትግራይ ክልልን እንደማይጨምር በሪፖርቱ የተገለጸ መሆኑንና በተሳሳተ አረዳድ ስለተሰራጨው የተሳሳተ መረጃና ተያያዥ ጉዳዮች በተመለከተ ኮሚሽኑ ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር እንደሚነጋገር ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።   በዚህም መሠረት ኮሚሽኑ ከትግራይ…
ተጨማሪ ያንብቡ
ኢሰመኮ ሰሞኑን ያወጣሁትን መግለጫ ላይ ማስተካከያ አደርጋለሁ ብሏል፡፡

ኢሰመኮ ሰሞኑን ያወጣሁትን መግለጫ ላይ ማስተካከያ አደርጋለሁ ብሏል፡፡

አርብ ጥቅምት 15 /2016 ኢሰመኮ ሰሞኑን ባወጣው ኹለተኛው አገር ዓቀፍ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ሪፖርት ትግራይን አስመልክቶ የተሳሳተ መረጃ ማካተቱን ትናንት ምሽት ባወጣው እርማት አስታውቋል። ኮሚሽኑ በሪፖርቱ፣ በሰሜኑ ጦርነት የተፈናቀሉ በርካታ ሰዎች ወደቀያቸው እንደተመለሱና ጅምሩ መልካም ርምጃ እንደኾነ ገልጦ ነበር። ለሪፖርቱ የተሠራው ጥናት ትግራይን አያካትትም ነበር ያለው ኮሚሽኑ፣ የተሳሳተውን መረጃ ከክልሉ አስተዳደር ጋር በመተባበር እንደሚያጣራው ገልጧል።
ተጨማሪ ያንብቡ

በኢትዮጵያ ዓለማቀፉ የሰብዓዊ መብቶች መርማሪ ኮሚሽን በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ወንጀል የፈጸሙ አካላት በአለም አቀፍ ፍ/ቤቶች ተጠያቂ እንዲሆኑ ጠየቀ፡፡

አርብ ጥቅምት 15 /2016 በኢትዮጵያ ዓለማቀፉ የሰብዓዊ መብቶች መርማሪ ኮሚሽን አገራትና ተቋማት በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ወንጀሎችን የፈጸሙ አካላት በዓለማቀፍ ፍርድ ቤቶች ጭምር ተጠያቂ እንዲኾኑ ጥረት እንዲያደርጉ ረቡዕ'ለት ለተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ባቀረበው ሪፖርት ጠይቋል። ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ የኢትዮጵያን የሰብዓዊ መብት ኹኔታ መከታተሉንና ለጦርነቱ ተጎጂዎች ድጋፍ መስጠቱን እንዳያቋርጥም ኮሚሽኑ አሳስቧል። ኮሚሽኑ፣ በአገሪቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በቀጠሉበት ወቅት ቆይታ ጊዜው እንዲያበቃ መደረጉ ስህተት መኾኑንም ለተመድ ጠቅላላ ጉባዔ ገልጧል።
ተጨማሪ ያንብቡ
በኢትዮጵያ የሚገኙ ስደተኞች ከማህበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው መኖር የሚችሉበት የቃል ኪዳን ሰነድ መዘጋጀቱ ተገለጸ

በኢትዮጵያ የሚገኙ ስደተኞች ከማህበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው መኖር የሚችሉበት የቃል ኪዳን ሰነድ መዘጋጀቱ ተገለጸ

ሐሙስ ጥቅምት 15 ቀን 2016 በኢትዮጵያ የሚገኙ ስደተኞች ከማህበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው መኖር የሚችሉበት የቃል ኪዳን ሰነድ መዘጋጀቱን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገልጸዋል። በስዊዘርላንድ ጀኔቭ በሚካሄደው ዓለም አቀፍ የስደተኞች ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ የምታቀርበውን ስድስት አዲስ የቃል ኪዳን ሰነድ ለማጽደቅ የተዘጋጀ የከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፤ ኢትዮጵያ አሁን ላይ ከተለያዩ አገራት የመጡ ከ1 ሚሊዮን በላይ ስደተኞችን ተቀብላ በማስተናገድ ላይ ትገኛለች ብለዋል። በኢትዮጵያ የሚገኙ ስደተኞችም ከማህበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው መኖር የሚችሉበት የቃል ኪዳን ሰነድ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። እኤአ በ2019 በተካሄደው ዓለም አቀፍ የስደተኞች…
ተጨማሪ ያንብቡ