ያገባኛል

በአምስት የኢትዮጵያ ክልሎች የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ተባብሰው መቀጠላቸውን ኢሰመኮ በምርመራ ማረጋገጡን አስታወቀ

በአምስት የኢትዮጵያ ክልሎች የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ተባብሰው መቀጠላቸውን ኢሰመኮ በምርመራ ማረጋገጡን አስታወቀ

      በ-እታገኘሁ መኮነን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብች ኮሚሽን በኢትዮጵያ በአማራ ፣በኦሮሚያ ፣በማእከላዊ ኢትዮጵያ ፣በደቡብ ኢትዮጵያ እና በጋምቤላ ክልል ከሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. እስከ መስከረም ወር 2017 ዓ.ም. የተፈፀሙ  የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ዙሪያ ሪፖርት አውጥቷል፡፡ኮሚሽኑ በሪፖርቱ  በኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች፣ ሥጋቶች እና አሳሳቢ ሁኔታዎች መኖራቸው እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ይህ የሩብ ዓመት የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት ግን በተለይ በግጭት ዐውድ ውስጥ ባሉ አካባቢዎች ላይ ልዩ ትኩረት በማድረግ በዋነኝነት ከፍተኛ በሆኑ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችና አሳሳቢነታቸው በቀጠሉ ጉዳዮች ላይ አተኩሮ የተሰራና  ለሰብአዊ መብቶች ሁኔታ መሻሻል ምክረ ሐሳቦችን የሚያቀርብ ነው ብሏል።  ሪፖርቱ በዳሰሳቸው አካባቢዎች በነጻነት ተንቀሳቅሶ የተሟላ ክትትልና ምርመራ ለማካሄድ ምቹ ሁኔታ ባለመኖሩ፣ በተቻለ መጠን…
ተጨማሪ ያንብቡ
“ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ” የተሰኘው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት፤ በኪነ ጥበብ ባለሙያዎች እና በጋዜጠኞች ላይ የሚፈጸመው  እስር አሳስቦኛል አለ

“ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ” የተሰኘው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት፤ በኪነ ጥበብ ባለሙያዎች እና በጋዜጠኞች ላይ የሚፈጸመው  እስር አሳስቦኛል አለ

 “ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ” የተሰኘው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት በጋዜጠኞች፣ በኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ በማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እንዲሁም በፖለቲከኞች ላይ እየተፈጸመ ያለው “የዘፈቀደ እስር” እንዳሳሰበው ትናንት አርብ ግንቦት 30፤ 2016 ባወጣው መግለጫ አሳውቋል ። እርምጃው “በአሳሳቢ ሁኔታ እየጠበበ የመጣውን የመገናኛ ብዙሃን ነጻነት እና ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት የማፈን አዝማሚያን የሚያመለክት ነው” ብሏል ድርጅቱ። ሀገር በቀሉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት በኢትዮጵያ በርካቶች ስለሚጋፈጧቸው እውነታዎች የዘገቡ እና አመለካከታቸውን ያንጸባረቁ ግለሰቦች መታሰራቸውን አስታውቋል። የግለሰቦቹ መታሰር፤ መሰረታዊ የሆኑትን የሰብዓዊ መብቶች “በግልጽ የሚጥስ” መሆኑን በመጥቀስም ድርጅቱ ተችቷል። ኪነ ጥበብ በሰብአዊ መብት ዙሪያ ያለን ግንዛቤን ለማሳደግ “ወሳኝ ሚና” እንደሚጫወት የጠቀሰው የድርጅቱ መግለጫ፤ በኪነ…
ተጨማሪ ያንብቡ
መንግስት በፈፀማቸው  የድሮን ጥቃቶች 10 ሰዎች መገደላቸውን ኢሰመኮ ገለጸ

መንግስት በፈፀማቸው  የድሮን ጥቃቶች 10 ሰዎች መገደላቸውን ኢሰመኮ ገለጸ

በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ በአፋር፣ በሶማሊ፣ በሲዳማ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ እና በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎችና በአዲስ አበባ ከተማ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን አስታወቀ። ኮሚሽኑ ባወጣው የሰብዓዊ መብት ሪፖርት መንግስት ታህሳስ እና ግንቦት ላይ በፈጸማቸው ሁለት የድሮን ጥቃቶች 10 ሰዎች ሲገደሉ ከ10 በላይ ቆስለዋል ብሏል ፡፡ ከሕግ ውጭ ግድያ፣ የሲቪል ሰዎች ሞት፣ የአካል ጉዳት፣ የንብረት ውድመትና ዘረፋ፣ የዘፈቀደ፣ የጅምላና የተራዘመ እስራትና የተፋጠነ ፍትሕ እጦት፣ አስገድዶ መሰወር፣ እገታ፣ እና የሀገር ውስጥ መፈናቀል እጅግ አሳሳቢ ሆነው የቀጠሉ የመብት ጥሰቶች መሆናቸው ተገልጿል። ኮሚሽኑ በጸጥታ ችግር እና ከመንግስት ተገቢውን ትብብር ባለማግኘት እንዲሁም በሌሎች ምክንያቶች የዘገዩ ምርመራዎች በሂደት…
ተጨማሪ ያንብቡ
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ በመንግስት ጫና እየተደረገበት እንደሆነ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ በመንግስት ጫና እየተደረገበት እንደሆነ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) መንግስት ከፍተኛ ጥቃትና ጫና እየፈጸመበት እንደሆነ ባወጣው መግለጫ ገልጿል፡፡ ኢሰመጎ በመግለጫው በመንግስት እየደረሰበት ያለው ጥቃት እና ጫና አስጊ ደረጃ ላይ መድረሱን  አሳውቋል። ጉባኤው በተለያዩ ጊዜ ተፈጽመውብኛል ያላቸው ጥቃቶች እና ከፍተኛ ጫናዎች በመግለጫው ላይ የዘረዘረ ሲሆን በተቋሙ አመራር ላይ በመንግስት የደህንነት ሰዎች የሚፈጸም ክትትል ፣ ዛቻ እና ማስፈራሪያ እየጨመረ መምጣታቸውን አስታውቋል፡፡ እንዲሁም የሰብዓዊ መብት ክትትል ስራችሁን ካላቆማችሁ ፤ መንግሥትን በሰብዓዊ መብት ጥሰት መወንጀል ካላቆማችሁ  ‘ ዋጋ ትከፍላላችሁ ‘ የሚል ዛቻ እየደረሰበት መሆኑን ገልጿል፡፡ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የምርመራ ስራ በሚሰሩ ሰራተኞች ላይ የመንግስት ጸጥታ አካላት አካላዊ ጥቃት ማድረስ፣ መሳደብ፣ ማንገላታት፣ ስራቸውን እንዲያቆሙ ማስፈራራት…
ተጨማሪ ያንብቡ
የኪነጥበብ ስራዎችን ማገድ ሃሳብን በነፃነት መግለጽ መብትን ማገድ ነው-የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል  

የኪነጥበብ ስራዎችን ማገድ ሃሳብን በነፃነት መግለጽ መብትን ማገድ ነው-የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል  

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል  ዋና ዳይሬክተር አቶ ያሬድ ሀይለመስቀል   የኪነ ጥበብ ስራዎች ሀሳብን በነጻነት የመግለጫ መንገድ በመሆናቸው  ከጥቃት ሊጠበቁ እና ባለሙያዎችም ለእስር ሊዳረጉ አይገባም ብለዋል፡፡ መንግስት ለኪነ ጥበብ ሙያ እና ባለሙያዎች ልዩ ጥበቃ ሊያደርግ ይገባል ያሉት አቶ ያሬድ ኪነ-ጥበብ ለሰብአዊ መብቶች ግንዛቤ መዳበር፣ መጎልበት እንዲሁም  መስፋፋት እና መከበር ያለው ጉልህ ሚና እጅግ የላቀ ነው ብለዋል፡፡ በተለይም የኪነ-ጥበብ መድረኮች እና ባለሞያዎች በሙዚቃ፣ በቲያትር፣ በግጥም፣ በስዕል እና በቅርፃቅርፅ መልክ የሚያንጸባርቋቸው ሃሳቦች የዜጎች ሃሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት መገለጫዎች እንደሆኑ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። እነዚህ የኪነ-ጥበብ ዘርፎች ለአንድ ማህበረሰብ የደስታም ሆነ የብሶት ሃሳቦቹን የሚገልጽባቸው መንገዶች የመሆናቸውን ያህል በአገር አስተዳደር ኃላፊነት ላይ…
ተጨማሪ ያንብቡ
የሴት ልጅ ግርዛትን የተመለከተው አወዛጋቢው የኢትዮጵያ ዑለማዎች ውሳኔ

የሴት ልጅ ግርዛትን የተመለከተው አወዛጋቢው የኢትዮጵያ ዑለማዎች ውሳኔ

የኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ የዑለማ ጉባዔ፣ የ2ኛ ዓመት መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔን በማስመልከት የወጣው መግለጫ በማኅበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ሆኗል። የኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ ላይ ጥር 22 ቀን፣ 2016 ዓ. ም. ባወጣው መግለጫ ላይ የሴት ልጅ ግርዛትን በተመለከተ በቁጥር 12 እና 13 ላይ የሰፈረው ውሳኔ ከሴቶች መብት እንዲሁም ከኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት አንጻር ተቃርኖ እንዳለው እንደ “አዲስ ፓወር ሃውስ’’ እና “አርቲክል 35” ያሉ በሴቶች መብት ላይ የሚሠሩ ንቅናቄዎች በማኅበራዊ ሚዲያ ገጾቻቸው ድምጻቸውን እያስተጋቡ ነው። በመግለጫው ላይ በቁጥር 12 እና 13 የሰፈሩት ውሳኔዎች እንደሚከተለው ተቀምጠዋል። እነዚህንና ሌሎች በመግለጫው የተካተቱ “ውሳኔዎችና ፈትዋዎችን የእስልምና ጉዳዮች…
ተጨማሪ ያንብቡ
“ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸው ዜጎች የሥነ ልቦና አገልግሎት፣ የሕግና የመልሶ ማቋቋም ድጋፍ እየተደረገላቸው አይደለም፡፡” ኢሰመኮ

“ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸው ዜጎች የሥነ ልቦና አገልግሎት፣ የሕግና የመልሶ ማቋቋም ድጋፍ እየተደረገላቸው አይደለም፡፡” ኢሰመኮ

የካቲት 13/2016 እታገኘሁ መኮነን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በትግራይ ክልል አምስት ዞኖች አስተዳደሮች ውሰጥ ሰብዓዊ መብትና ሰብዓዊ ቀውስን በተመለከተ አካሄድኩት ያለውን የምርመራ ሪፖርት ማክሰኞ የካቲት 12 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ በሪፖርቱም በትግራይ ክልል በተለያየ ጊዜ ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸው ዜጎች የሥነ ልቦና አገልግሎት፣ የሕግና የመልሶ ማቋቋም ድጋፍ እየተደረገላቸው አለመሆኑን አስታውቋል፡፡ አብዛኞቹ  ጥቃቶች የተፈጸሙት ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ ነው ያለው ኮሚሽኑ በተለይ ደግሞ ጥቃቱ ተባብሶ የሚታየው በኤርትራና በአማራ ኃይሎች ቁጥጥር ስር በሚገኙ  አካባቢዎች እንደሆነ ተገልጽዋል፡፡ ጾታዊ ጥቃት የሚደርስባቸው ሴቶች በከፍተኛ ሁኔታ መገለል ስሚደርስባቸው ከማህበረሰቡ እየራቁ እና ለስነልቦና ጉዳት እየተዳረጉም ነው ሲል ኮሚሽኑ የችግሩን ስፋት ትናንት ባወጣው ሪፖርቱ…
ተጨማሪ ያንብቡ
“…..በወልቂጤ ተከስቶ በነበረው ሁከት ማጣራት በማድረግ ተጎጂዎች ሊካሱ ይገባል።” ዶ/ር ዳንኤል በቀለ

“…..በወልቂጤ ተከስቶ በነበረው ሁከት ማጣራት በማድረግ ተጎጂዎች ሊካሱ ይገባል።” ዶ/ር ዳንኤል በቀለ

16/04/2016 የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ በጉራጌ ዞን እና በቀቤና ልዩ ወረዳ መካከል የነበረውን አለመግባባት ተከትሎ ባወጣው ሪፖርት እንዳስነበበው ከጥቅምት 2 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ የተከሰተውን የጸጥታ መደፍረስና ያስከተለውን ጉዳት ከአካባቢው ነዋሪዎች በቀረበለት አቤቱታ መነሻነት ከጥቅምት 20 እስከ 25 ቀን 2016 ዓ.ም. በቦታው በመገኘት ምርመራ ማከናወኑን ገልጿል። ኮሚሽኑ ከተጎጂዎች እና ምስክሮች ጋር 22 ቃለ-መጠይቆች አድርጓል ያለው ሪፖርቱ ከጉራጌ ዞን፣ ከወልቂጤ ከተማ አስተዳደር እና ከቀቤና ልዩ ወረዳ የሥራ ኃላፊዎች እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ማድረጉን ገልጿል። ዘረፋ እና ውድመት የደረሰባቸው እና የግል እና የመንግሥት ተቋማትን ኮሚሽኑ ተዘዋውሮ የጎበኘ ሲሆን ተጎጂዎች ሕክምና ካገኙባቸው የሕክምና ተቋማት…
ተጨማሪ ያንብቡ
“በግጭቱ እየደረሰ ያለው እጅግ አሠቃቂ ጉዳት ከዚህ የበለጠ ከመባባሱ እና የበለጠ ጉዳት ከማድረሱ በፊት መፍትሔ ይሰጠው ” ኢሰመኮ

“በግጭቱ እየደረሰ ያለው እጅግ አሠቃቂ ጉዳት ከዚህ የበለጠ ከመባባሱ እና የበለጠ ጉዳት ከማድረሱ በፊት መፍትሔ ይሰጠው ” ኢሰመኮ

አሸናፊ አሰበ 27/03/2016 የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ ክልል፣ በአዊ ብሔረሰብ ዞን፣ በአየሁ ጓጉሳ ወረዳ እና በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ቡሬ ዙሪያ ወረዳ፤ እንዲሁም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ አሶሳ ዞን፣ ኦዳ ብልድግሉ ወረዳ፤ በተጨማሪም በኦሮሚያ ክልል፣ በአርሲ ዞን፣ ሸርካ ወረዳ እና በቄለም ወለጋ ዞን፣ ጊዳሚ ወረዳ በሲቪል ሰዎች ላይ የተፈጸሙ ጥቃቶችን በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ አሶሳ ዞን፣ ኦዳ ብልድግሉ ወረዳ ሥር በሚገኙ ቤልሚሊ፣ አልከሻፊ እና ቤላደሩ ቀበሌዎች በሚኖሩ የቤኒሻንጉል ብሔር ተወላጆች እና አብረው በሚኖሩት የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች ላይ ኅዳር 19 ቀን 2016 ዓ.ም. ከንጋቱ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 5፡00 ሰዓት አካባቢ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶ…
ተጨማሪ ያንብቡ
በማደግ ላይ ላሉ ሀገራት የሚውል ‘የአየር ንብረት ፈንድ’ እንዲንቀሳቀስ ስምምነት ላይ ተደረሰ።

በማደግ ላይ ላሉ ሀገራት የሚውል ‘የአየር ንብረት ፈንድ’ እንዲንቀሳቀስ ስምምነት ላይ ተደረሰ።

ህዳር 22/2016 የኮፕ28 ስብሰባ ፕሬዝዳንት ዶክተር  ሱልጣን ቢን አህመድ አልጃብር በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የበለጠ ተጎጂ ለሆኑ ሀገራት የሚውል 'የአየር ንብረት ፈንድ' እንዲንቀሳቀስ ሀገራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታውቀዋል። የአረብ ኢምሬትስ አመራር ተጋላጭ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች እና ሀገራት እንዲረዱ በማድረግ አለምአቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ ጥረቶች እንዲጠናከሩ እየሰራ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል። የአረብ ኢምሬትስ የኢንዱስትሪ እና አድቫንስድ ቴክኖሎጂ ሚኒስትር እና የኮፕ28 ስብሰባ ፕሬዝደንት ዶክተር  ሱልጣን ቢን አህመድ አልጃብር ዘላቂ የኢኮኖሚ ልማትን ለማሳካት ተጋላጭ የሆኑ ሀገራት እና ማህበረሰቦች እንዲረዱ በተነሳሽነት ብዙ እርምጃዎችን መወሰዳቸውን ተናግረዋል። የኢምሬትስ ዜና አገልግሎት(ዋም) እንደዘገበው ዶክተር አልጃብር ይህን ያሉት በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ለችግር ለተጋለጡ በማደግ…
ተጨማሪ ያንብቡ