ሃቅ ፈላጊ

ሐቅን ፍለጋ

ሐቅን ፍለጋ

መረጃ የምናገኝበት አማራጭ አድጓል፡፡የምናገኛቸው መረጃዎች በሙሉ ግን የተጣሩ እና ትክክለኛ  መሆናቸውን  የማረጋገጥ ልማዳችን ግን ገና ነው፡፡የጋዜጠኛ ሥራ መሰረቱ እውነታን በማጣራት እና በማረጋገጥ ላይ የተመሰረተ ቢሆንም ተሰራጭተው የምናገኛቸው መረጃዎች ሁሉ ግን በጋዜጠኞች እና ኃላፊነት በሚሰማቸው መገናኛ ብዙሃን የተዘጋጁ አይደሉም። አሁን ኢትዮጵያን ከሚፈትኑ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ የተዛቡ መረጃዎች  ስርጭት ነው፡፡በተለያዩ ጊዜዎች የተከሰቱ ግጭቶችን  እና ወቅታዊ ጉዳዮችን ተከትሎ ደግሞ እነዚህ የመረጃ መዛባቶች እና ሀሰተኛ መረጃዎች ይበራከታሉ፡፡ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ሃገራዊ ምርጫ ለማድረግ ስትዘጋጅ አንደኛው ስጋቷ የነበረው ይሀው ጉዳይ ነበር።የምርጫ ወቅቶች የሚኖሩ መረጃዎች የመራጮች ውሳኔ ላይ በቀጥታም በተዘዋዋሪም ተፅእኖ ይኖራቸዋል፡፡ አዲስ ጊዜ ሐቅ ለማጣራት የእውነት ማጣሪያ አምድን  በድረገጹ አዘጋጅቷል፡፡ይህ የእውነት ማጣሪያ…
ተጨማሪ ያንብቡ
በምርጫ ወቅት እውነት ሲጣራ

በምርጫ ወቅት እውነት ሲጣራ

የሀሰተኛ መረጃዎች ስርጭት ሁሉም በተለያየ መልኩ ሊኖሩ ይችላሉ።ሀገራት ምርጫ በሚያደርጉበት እና ግጭቶች በሚከሰቱበት ወቅት ሀሰተኛ መረጃዎች ከሌላው ጊዜ በተለየ ጨምረው ይስተዋላሉ።እነዚህ በተለያዩ ይዘቶች የሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎች ማጣሪያ ስይደረግባቸው ከቀጠሉ ወቅት እየጠበቁ እንደ አዲስ ሊጋሩ ይችላሉ። በ7ኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ወቅት ከተሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎች መካከል ከአውድ ውጪ ጥቅም ላይ የዋሉ  ምስሎች፣በሰው ሰራሽ አስተውሎት(AI) የተፈጠሩ ምስሎች እና በስላቅ መልክ የተሰራጩ መረጃዎች ይገኙበታል። ከአውድ ውጪ፡ ይህ ምስል በግንቦት ወር 2018 ዓ.ም ደብረብርሃን ውስጥ የተዘጋ መንገድን አያሳይም  ምስሉ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ይገኛል።ይህ በግንቦት ወር 2018 ዓ.ም ደብረብርሃን ውስጥ የተዘጋ መንገድን ያሳያል በሚል ኤክስ (የቀድሞ ትዊተር) ላይ ከምስል…
ተጨማሪ ያንብቡ
የብልፅግና ፓርቲ ‘የሚዲያ ሠራዊት’ አባላት በሐሰተኛ መረጃ ሥርጭት እና አሳሳች የፌስቡክ ዘመቻዎች ላይ መሳተፋቸውን ቢቢሲ በምርመራ ማረጋገጡን ዘግቧል፡፡

የብልፅግና ፓርቲ ‘የሚዲያ ሠራዊት’ አባላት በሐሰተኛ መረጃ ሥርጭት እና አሳሳች የፌስቡክ ዘመቻዎች ላይ መሳተፋቸውን ቢቢሲ በምርመራ ማረጋገጡን ዘግቧል፡፡

በገዢው ብልፅግና ፓርቲ በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ስር የሚንቀሳቀሱ እና ‘የሚዲያ ሠራዊት’ የሚል መጠሪያ ያላቸው የፓርቲው አባላት፤ መንግሥትን በሚተቹ እና በሚቃወሙ ግለሰቦች ላይ በፌስቡክ በተደረጉ የሐሰተኛ መረጃ እንዲሁም ‘የጥላቻ ንግግር’ ተብለው ሊቆጠሩ የሚችሉ ጽሑፎች እና ምስሎች ሥርጭት ላይ እንደተሳተፉ ቢቢሲ  በምርመራ ማረጋገጡን ዘግቧል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወረዳ አመራሮችም በፓርቲው የወረዳ መዋቅሮች ትዕዛዝ በተለይም የመንግሥትን ገፅታ በሰው ሰራሽ መንገድ ለመገንባት ፌስቡክ ላይ በሚደረጉ አሳሳች ዘመቻዎች ላይ እንደሚሳተፉም ተናግሯል፡፡ ቢቢሲ ለዚህ ዘገባ በአዲስ አበባ ከተማ የወረዳ አመራር፣ የፓርቲ አባል እንዲሁም በከተማዋ እና በፌደራል መንግሥት መሥሪያ ቤቶች ውስጥ የሚሰሩ የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች  አነጋግሬያለሁ ያለ…
ተጨማሪ ያንብቡ